申命记 15 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

申命记 15:1-23

安息年

1“每逢第七年末,你们要免除他人的债务。 2你们要这样做,所有债主都要免除同胞所欠的债务,不可向他们追讨,因为宣布免除债务的是耶和华。 3你们可以向外族人讨债,但无论同胞欠你什么债务,都要免除。 4-5只要你们听从你们上帝耶和华的话,谨遵我今天吩咐你们的诫命,祂必使你们在这片祂赐给你们作产业的土地上蒙福,你们中间不会有穷人。 6你们的上帝耶和华必照祂的应许赐福给你们,你们必借贷给多国,却不需要向他们借贷。你们必统治多国,却不被他们统治。

7“在进入你们的上帝耶和华将要赐给你们的土地后,如果你们居住的城中有贫穷的同胞,你们不可硬着心肠拒施援手。 8他们所需要的,你们要慷慨地借给他们。 9你们要谨慎,不可因为免除债务的第七年将近,就心怀恶念,对贫穷同胞冷眼相待,拒施援手。否则,他会求告耶和华,那时你们便有罪了。 10你们要慷慨给予,并且无怨无悔,因为耶和华必在你们所做的一切事上赐福给你们。 11你们居住的地方总会有穷人,所以我吩咐你们要慷慨地帮助贫穷或有需要的同胞。

12“如果你们的希伯来同胞,不论男女,卖身给你们做奴隶,他们要服侍你们六年,到第七年,你们要给他们自由。 13你们不可让他们空手离去, 14要慷慨地把你们的上帝耶和华赐给你们的羊、五谷和酒分给他们。 15要记住,你们曾在埃及做奴隶,你们的上帝耶和华拯救了你们。所以,我今天吩咐你们这样做。 16如果你们的奴隶因为爱你们和你们的家人,与你们相处融洽,不愿意离去, 17你们就要让他靠在门上,用锥子在他耳朵上扎个洞,他便终身成为你们的奴隶。对待婢女也要这样。 18你们释放奴隶时,不要不情愿,因为他们服侍你们六年,所做的是普通雇工的两倍。而且,你们的上帝耶和华也会在你们所做的一切事上赐福给你们。

头生的牛羊

19“你们要把头生的公牛和公羊分别出来,献给你们的上帝耶和华。不可用头生的公牛耕田,也不要剪头生公羊的毛。 20每年,你们全家要去你们的上帝耶和华选定的地方,在祂面前吃这些头生的牛羊。 21如果这些牛羊有什么残疾,如瘸腿、瞎眼或其他残疾,就不可献给你们的上帝耶和华。 22要在你们的城里吃这些牛羊。洁净的人和不洁净的人都可以吃,就像吃羚羊和鹿一样。 23但不可吃它们的血,要把血倒在地上,像倒水一样。

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 15:1-23

ዕዳ የሚተውበት ዓመት

15፥1-11 ተጓ ምብ – ዘሌ 25፥8-38

1በየሰባቱ ዓመት መጨረሻ የዕዳ ምሕረት አድርግ። 2አፈጻጸሙም እንደሚከተለው ነው፤ እያንዳንዱ አበዳሪ ለእስራኤላዊ ባልንጀራው ያበደረውን ይተውለት፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) የዕዳ ምሕረት ዐውጇልና፣ አበዳሪው፣ እስራኤላዊ ባልንጀራውን ወይም ወንድሙን ዕዳውን እንዲከፍለው አይጠይቀው። 3ለባዕድ ያበደርኸውን መጠየቅ ትችላለህ፤ ወንድምህ ከአንተ የተበደረውን ማናቸውንም ዕዳ ግን ተወው። 4ይሁን እንጂ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ትወርሳት ዘንድ ርስት አድርጎ በሚሰጥህ ምድር ውስጥ አብዝቶ ስለሚባርክህ፣ በመካከልህ ድኻ አይኖርም፤ 5ይህ የሚሆነውም ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፈጽመህ ስትታዘዝና ዛሬ የምሰጥህን እነዚህን ትእዛዞች ሁሉ በጥንቃቄ ስትከተል ብቻ ነው። 6አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት ስለሚባርክህ፣ አንተ ለብዙ አሕዛብ ታበድራለህ እንጂ ከማንም አትበደርም፤ ብዙ አሕዛብን ትገዛለህ እንጂ ማንም አንተን አይገዛህም።

7አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሚሰጥህ ምድር ላይ ካሉት ከተሞች በአንዲቱ ውስጥ ድኻ ቢኖር፣ በድኻ ወንድምህ ላይ ልብህን አታጨክንበት፤ ወይም እጅህን ወደ ኋላ አትሰብስብበት። 8ይልቁንስ እጅህን ፍታለት፤ የሚያስፈልገውንም ሁሉ ቅር ሳይልህ አበድረው። 9“ዕዳ የሚሠረዝበት ሰባተኛው ዓመት ተቃርቧል” የሚል ክፉ ሐሳብ ዐድሮብህ፣ በችግረኛ ወንድምህ ላይ እንዳትጨክንና ምንም ሳትሰጠው እንዳትቀር፣ እርሱም በአንተ ላይ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጮኾ በደለኛ እንዳትሆን ተጠንቀቅ! 10በልግስና ስጠው፤ ስትሰጠውም ልብህ አይጸጸት፤ ከዚህም የተነሣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሥራህ ሁሉና እጅህ ባረፈበት በማናቸውም ነገር ይባርክሃል። 11በምድሪቱ ላይ ድኾች ምንጊዜም አይጠፉም፤ ስለዚህ በዚያ ለሚኖሩ ወንድሞችህ፣ ለድኾችና ለችግረኞች እጅህን እንድትዘረጋ አዝዝሃለሁ።

አገልጋዮችን ዐርነት ማውጣት

15፥12-18 ተጓ ምብ – ዘፀ 21፥2-6

15፥12-18 ተጓ ምብ – ዘሌ 25፥38-55

12ወገንህ የሆነ ዕብራዊ ወንድን ወይም ሴትን ገዝተህ ስድስት ዓመት ካገለገለህ፣ በሰባተኛው ዓመት ዐርነት አውጣው። 13በምታሰናብተውም ጊዜ ባዶ እጁን አትስደደው። 14ከመንጋህ፣ ከዐውድማህና ከወይን መጭመቂያህ በልግስና ስጠው፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በባረከህ መጠን ስጠው። 15አንተም ራስህ በግብፅ ባሪያ እንደ ነበርህና አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንደ ተቤዠህ አስታውስ፤ ይህን ትእዛዝ ዛሬ የምሰጥህም በዚሁ ምክንያት ነው።

16ነገር ግን አገልጋይህ፣ አንተንና ቤተ ሰብህን ከመውደዱና ከአንተም ጋር ደስተኛ ሆኖ ከመኖሩ የተነሣ፣ “ከአንተ መለየት አልፈልግም” ቢልህ፣ 17ጆሮውን ከቤትህ መዝጊያ ላይ በማስደገፍ በወስፌ ትበሳዋለህ፤ ከዚያም ዕድሜ ልኩን አገልጋይህ ይሆናል። በሴት አገልጋይህም ላይ እንደዚሁ አድርግ።

18አገልጋይህን ዐርነት ማውጣቱ ከባድ መስሎ አይታይህ፤ የስድስት ዓመት አገልግሎቱ፣ አንድ የቅጥር ሠራተኛ የሚሰጠው አገልግሎት ዕጥፍ ነውና። አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በምታደርገው ነገር ሁሉ ይባርክሃል።

የእንስሳት በኵራት

19የቀንድ ከብት፣ የበግና የፍየል መንጋዎችህን ተባዕት በኵር ሁሉ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ቀድስ። የበሬህን በኵር አትሥራበት፤ የበግህንም በኵር አትሸልት፤ 20እርሱ በሚመርጠው ስፍራ አንተና ቤተ ሰብህ በየዓመቱ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ትበሉታላችሁ። 21አንድ እንስሳ እንከን ካለበት፣ ዐንካሳ ወይም ዕውር ወይም ደግሞ ማናቸውም ዐይነት ከባድ ጕድለት ያለበት ከሆነ፣ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አትሠዋው፤ 22በየከተሞችህም ትበላዋለህ፤ በሥርዐቱ መሠረት ንጹሕ የሆነውም ሆነ ያልሆነው ሰው፣ እንደ ድኵላ ወይም እንደ ዋላ ይበላዋል። 23ደሙን ግን እንደ ውሃ መሬት ላይ አፍስሰው እንጂ አትብላው።