撒迦利亚书 10 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

撒迦利亚书 10:1-12

耶和华应许拯救以色列

1要在春季向耶和华求雨。

祂创造雷雨,

为世人降下甘霖,

使田间长出青翠之物。

2因为神像说的是虚言,

占卜者讲的是谎话,

他们说的是假梦,

他们的安慰是空的。

所以人们如迷失的羊,

因没有牧人而受苦。

3“我必向牧人发怒,

我必惩罚这些首领10:3 首领”希伯来文作“公山羊”。

因为我——万军之耶和华必眷顾我的羊群犹大家,

我必使他们像战场上的骏马。

4房角石、帐篷的橛子、战弓,

以及所有掌权者必出自犹大

5他们必像战场上的勇士,

将仇敌践踏在街上的泥土中。

他们必争战,

因为耶和华与他们同在。

他们必使敌方的骑兵蒙羞。

6“我必使犹大家强盛,

我必拯救约瑟家。

我必带他们回到故土,

因为我怜悯他们。

他们必好像从未被我抛弃一样,

因为我是他们的上帝耶和华,

我必应允他们的祷告。

7以法莲人必如勇士,

他们必心里快乐,如同喝了酒,

他们的儿女见状也必快乐,

他们必因耶和华而欢心。

8“我必吹哨聚集他们,

因为我救赎了他们,

他们必像从前一样人数众多。

9虽然我把他们分散到列国,

他们必在远方想起我,

他们及其子女必得以幸存,

并且回到故土。

10我必从埃及领他们回到故土,

亚述招聚他们,

领他们到基列黎巴嫩

那里将不够他们居住。

11祂必经过苦海,

击打海浪,

尼罗河必干涸,

亚述的骄傲必扫地,

埃及的势力必灭没。

12我必让他们靠着我强盛,

他们必奉我的名行事。

这是耶和华说的。”

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 10:1-12

እግዚአብሔር ለይሁዳ ይጠነቀቃል

1የበልግ ዝናብ እንዲሰጣችሁ እግዚአብሔርን ጠይቁ፤

ማዕበሉን ደመና የሚያደርግ እግዚአብሔር ነው፤

እርሱ ለሰዎች በቂ ዝናብን፣

ለእያንዳንዱም የምድርን ተክል ይሰጣል።

2ተራፊም አሳሳች ነገር ይናገራል፤

ሟርተኞች የሐሰት ራእይ ያያሉ፤

የውሸት ሕልም ይናገራሉ፤

ከንቱ መጽናናት ይሰጣሉ፤

ስለዚህ ሕዝቡ እንደ በጎች ተቅበዘበዙ፤

እረኛ በማጣትም ተጨነቁ።

3“ቍጣዬ በእረኞች ላይ ነድዷል፤

መሪዎችንም እቀጣለሁ፤

እግዚአብሔር ጸባኦት፣

ለመንጋው ለይሁዳ ቤት ይጠነቀቃልና፤

በጦርነትም ጊዜ እንደ ክብሩ ፈረስ ያደርጋቸዋል።

4ከይሁዳ፣ የማእዘን ድንጋይ፣

የድንኳን ካስማ፣

የጦርነት ቀስት፣

ገዥም ሁሉ ይወጣል።

5ጠላትን መንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ ይረጋግጣሉ፤

በአንድነት10፥5 ወይም ሁሉም ገዦች በአንድነት ማለት ነው 5 እነርሱም እንደ ጦር ሰልፈኛ ይሆናሉ፤

እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ስለሆነ ተዋግተው፤

ፈረሰኞችን ያዋርዳሉ።

6“የይሁዳን ቤት አበረታለሁ፤

የዮሴፍንም ቤት እታደጋለሁ።

ስለምራራላቸው፣

ወደ ቦታቸው እመልሳቸዋለሁ፤

እነርሱም በእኔ እንዳልተተዉ ሰዎች

ይሆናሉ፤

እኔ አምላካቸው እግዚአብሔር ነኝና፣

ጸሎታቸውን እሰማለሁ።

7ኤፍሬማውያን እንደ ኀያላን ሰዎች ይሆናሉ፤

ልባቸውም የወይን ጠጅ እንደ ጠጣ ሰው ሐሤት ያደርጋል።

ልጆቻቸው ያዩታል፤ ደስተኛም ይሆናሉ፤

ልባቸውም በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል።

8በፉጨት እጠራቸዋለሁ፤

በአንድነት እሰበስባቸዋለሁ፤

በርግጥ እቤዣቸዋለሁ፤

እንደ ቀድሞው ይበዛሉ።

9በሕዝቦች መካከል ብበትናቸውም፣

በሩቅ ምድር ሆነው ያስቡኛል፤

እነርሱና ልጆቻቸው ተርፈው፣

በሕይወት ይመለሳሉ።

10ከግብፅ እመልሳቸዋለሁ፤

ከአሦርም እሰበስባቸዋለሁ፤

ወደ ገለዓድና ወደ ሊባኖስ አመጣቸዋለሁ፤

በቂ ስፍራም አይገኝላቸውም።

11በመከራ ባሕር ውስጥ ያልፋሉ፤

የባሕሩ ማዕበል ጸጥ ይላል፤

የአባይም ጥልቅ ሁሉ ይደርቃል።

የአሦር ትምክሕት ይዋረዳል፤

የግብፅም በትረ መንግሥት ያበቃል።

12በእግዚአብሔር አበረታቸዋለሁ፤

በስሙም ይመላለሳሉ”

ይላል እግዚአብሔር