弥迦书 1 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

弥迦书 1:1-16

1犹大约坦亚哈斯希西迦执政期间,耶和华把祂的话传给了摩利沙弥迦。他看到了有关撒玛利亚耶路撒冷的异象。

审判将临

2万民啊,

你们都要听!

大地和地上的万物啊,

你们要侧耳倾听!

主耶和华从祂的圣殿里作证指控你们。

3看啊,耶和华离开祂的居所,

从天降临,

脚踏大地的高处。

4群山在祂脚下熔化,

犹如火中的蜡;

山谷崩裂,

岩石如水沿山坡倾泻。

5这一切都是因为雅各的叛逆,

以色列家的罪恶。

雅各的叛逆在哪里呢?

岂不是在撒玛利亚吗?

犹大的丘坛在哪里呢?

岂不是在耶路撒冷吗?

6“所以,我耶和华要使撒玛利亚沦为荒野的废墟,

成为种葡萄的地方。

我要把她的石头抛进山谷,

直到露出她的根基。

7她所有的神像都要被打碎,

她所得的淫资都要化为灰烬;

我要毁灭她的一切偶像。

她以淫资得来的偶像,

也要被用作妓女的淫资。”

先知的哀伤

8为此,我要痛哭哀号,

我要赤身光脚而行,

像豺狼哀嚎,

如鸵鸟悲鸣。

9因为撒玛利亚的创伤无法救治,

已经祸及犹大

直逼我百姓的城门,直逼耶路撒冷

10不要在迦特宣扬,

也不要哭泣,

要在伯·亚弗拉的灰尘中打滚。

11沙斐的居民啊,

你们将赤身露体,

被羞辱地掳去。

撒南的居民不敢出城,

伯·以薛在痛哭,

你们已失去它的庇护。

12玛律的居民痛苦不堪,

渴望得到拯救,

因为耶和华已把灾难降到耶路撒冷的城门。

13拉吉的居民啊,

用骏马套车逃命吧!

是你们首先唆使锡安城犯罪,

在你们身上看到了以色列的罪恶。

14去向摩利设·迦特赠送告别礼物吧!

亚革悉人必令以色列诸王受骗上当。

15玛利沙的居民啊,

我要使征服者到你们那里。

以色列的领袖1:15 以色列的领袖”希伯来文是“以色列的荣耀”。要躲到亚杜兰

16犹大人啊,你们要剃光头发,

为你们所爱的儿女悲伤;

要剃得如秃鹰一样光秃,

因为他们要被掳到远方。

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 1:1-16

1በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሬታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል፣ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ ይህ ነው፤

2እናንተ አሕዛብ ሆይ፤ ሁላችሁም ስሙ፤

ምድር ሆይ፤ በውስጧም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ፤

ጌታ ከቅዱስ መቅደሱ፣

ልዑል እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይመሰክርባችኋል።

በሰማርያና በኢየሩሳሌም ላይ የተላለፈ ፍርድ

3እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያ ስፍራው ይመጣል፤

ወርዶም በምድር ከፍታዎች ላይ ይራመዳል።

4ተራሮች ከሥሩ ይቀልጣሉ፤

ሸለቆዎችም ይሰነጠቃሉ፤

በእሳት ፊት እንዳለ ሰም፣

በገደል ላይ እንደሚወርድ ፈሳሽ ይሆናሉ።

5ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣

ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው።

የያዕቆብ በደል ምንድን ነው?

ሰማርያ አይደለችምን?

የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው?

ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

6“ስለዚህ ሰማርያን የፍርስራሽ ክምር፣

ወይን የሚተከልባትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤

ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ አወርዳለሁ፤

መሠረቷንም ባዶ አደርጋለሁ።

7ጣዖቶቿ ሁሉ ይሰባበራሉ፤

ለቤተ መቅደሷ የቀረበው ገጸ በረከት በእሳት ይቃጠላል፤

ምስሎቿን ሁሉ እደመስሳለሁ፤

ገጸ በረከቷን በዝሙት ዐዳሪነት እንደ ሰበሰበች ሁሉ፣

አሁንም ገጸ በረከቷ የዝሙት ዐዳሪነት ዋጋ መቀበያ ይሆናል።”

ልቅሶና ሐዘን

8በዚህ ምክንያት አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይም እላለሁ፤

ባዶ እግሬንና ዕርቃኔን እሄዳለሁ፤

እንደ ቀበሮ አላዝናለሁ፤

እንደ ጕጕትም አቃስታለሁ።

9ቍስሏ የማይሽር ነውና፤

ለይሁዳ ተርፏል፤

እስከ ሕዝቤ መግቢያ በር፣

እስከ ኢየሩሳሌም እንኳ ደርሷል።

10በጌት1፥10 ጌት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ አውራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። አታውሩት፤

ከቶም አታልቅሱ1፥10 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ሲስማማ፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን በአኮ ላይ አታልቅሱ ይላል። በአኮ የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አለቀሰ ከሚለው የዕብራይስጡ ቃል ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው።

በቤትዓፍራ1፥10 ቤትዓፍራ ትርጕሙ የትቢያ ቤት ማለት ነው።

በትቢያ ላይ ተንከባለሉ።

11እናንት በሻፊር1፥11 ሻፊር ትርጕሙ አስደሳች ማለት ነው። የምትኖሩ፣

ዕርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ዕለፉ፤

በጸዓናን1፥11 ጸዓናን የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ውጣ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ

ከዚያ አይወጡም፤

ቤትዔጼል በሐዘን ላይ ናት፤

ለእናንተም መጠጊያ ልትሆን አትችልም።

12ከመከራው መገላገልን በመሻት፣

በማሮት1፥12 ማሮት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ መራራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ በሥቃይ

ይወራጫሉ፤

እስከ ኢየሩሳሌም በር ሳይቀር፣

ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቷልና።

13እናንት በለኪሶ1፥13 ለኪሶ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ቡድን ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ፣

ፈረሶችን ከሠረገላው ጋር አያይዙ፤

ለጽዮን ሴት ልጅ፣

የኀጢአት መጀመሪያ እናንት ነበራችሁ፤

የእስራኤል በደል

በእናንተ ዘንድ ተገኝቷልና።

14ስለዚህ እናንተ ለሞሬሼትጌት፣

ማጫ ትሰጣላችሁ፤

የአክዚብ1፥14 አክዚብ ትርጕሙ አታላይ ወይም ማታለል ማለት ነው። ከተማ፣

ለእስራኤል ነገሥታት መታለያ ትሆናለች።

15እናንት በመሪሳ1፥15 መሪሳ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ድል አድራጊ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ

ድል አድራጊ አመጣባችኋለሁ፤

ያ የእስራኤል ክብር የሆነው

ወደ ዓዶላም ይመጣል።

16ደስ ለምትሰኙባቸው ልጆቻችሁ፣

በሐዘን ራሳችሁን ተላጩ፤

ራሳችሁን እንደ አሞራ ራስ ተመለጡት፤

ከእናንተ በምርኮ ይወሰዳሉና።