帖撒罗尼迦后书 3 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

帖撒罗尼迦后书 3:1-18

请求代祷

1弟兄姊妹,最后我还要请你们为我们祷告,好使主的道像在你们那里一样迅速传开,受到尊崇, 2并使我们能避开那些邪恶的人,因为不是人人都有信心。

3主是信实的,祂必使你们刚强,保护你们脱离那恶者。 4我们靠着主深信你们现在遵行了我们的吩咐,而且以后还会继续遵行。

5愿主引导你们的心领悟上帝的爱和基督的坚忍。

不可游手好闲

6弟兄姊妹,现在我们奉主耶稣基督的名吩咐你们,要远离那些游手好闲、不遵守我们教导的信徒。 7你们自己知道应该怎样效法我们,因为我们在你们那里的时候,并没有懒懒散散, 8也没有白吃谁的饭,而是昼夜辛勤工作,免得成为你们任何人的负担。 9我们并不是没有权利接受供应,而是要给你们树立学习的榜样。 10我们在你们那里的时候,曾吩咐过你们:不肯工作的人没有资格吃饭。 11我们听说在你们当中有些人游手好闲,无所事事,却专管闲事。 12我们奉主耶稣基督的名吩咐并劝诫这些人要安分守己,自食其力。

13弟兄姊妹,你们要坚持行善,不要灰心。 14如果有人不听从这信上的教导,要注意提防他,不要和他来往,好使他羞愧。 15只是不可把他当作仇人,要像对待弟兄姊妹一样劝诫他。

问候

16愿平安之主随时随地亲自赐你们平安!愿主与你们同在! 17我保罗在这里亲笔问候你们,这是我的笔迹,我所有的信都以此为记号。

18愿我们主耶稣基督的恩典与你们众人同在!

New Amharic Standard Version

2 ተሰሎንቄ 3:1-18

ለጸሎት የቀረበ ጥያቄ

1በቀረውስ ወንድሞች ሆይ፤ በእናንተ ዘንድ እንደ ሆነው የጌታ ቃል በፍጥነት እንዲሠራጭና እንዲከበር ለእኛ ጸልዩልን፤ 2ደግሞም ሰው ሁሉ እምነት ያለው ስለማይሆን ከዐመፀኞችና ከክፉ ሰዎች እንድንድን ጸልዩልን። 3ጌታ ግን ታማኝ ነው፤ እርሱም ያበረታችኋል፤ ከክፉውም ይጠብቃችኋል። 4እኛ ያዘዝናችሁን አሁን አደረጋችሁ፤ ወደ ፊትም እንደምታደርጉ በጌታ እንታመናለን። 5ጌታ ልባችሁን ወደ እግዚአብሔር ፍቅርና ወደ ክርስቶስ ጽናት ይምራው።

ሥራ መፍታት እንደማይገባ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

6ወንድሞች ሆይ፤ ሥራ ፈት ከሆነና ከእኛ በተቀበላችሁት ትምህርት3፥6 ወይም ወግ መሠረት ከማይኖር ወንድም እንድትርቁ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን፤ 7የእኛን ምሳሌ እንዴት መከተል እንደሚገባችሁ እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁና። ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ ሥራ ፈቶች አልነበርንም፤ 8ደግሞም የማንንም እንጀራ በነጻ አልበላንም፤ ነገር ግን ከእናንተ በአንዳችሁም ላይ ሸክም እንዳንሆን ሌሊትና ቀን እንደክምና እንሠራ ነበር፤ 9ይህን ያደረግነው ምሳሌነታችንን እንድትከተሉ ብለን እንጂ የሚያስፈልገንን ነገር ከእናንተ ለማግኘት ሥልጣን ሳይኖረን ቀርቶ አይደለም። 10ከእናንተ ጋር በነበርንበት ጊዜ፣ “ሊሠራ የማይወድድ አይብላ” ብለን ይህን ትእዛዝ ሰጥተናችሁ ነበርና። 11ከእናንተ አንዳንዶች ሥራ ፈቶች እንደ ሆኑ ሰምተናል፤ እነርሱም ያለ ሥራ እየዞሩ በሰው ጕዳይ ጣልቃ የሚገቡ ናቸው። 12እንደዚህ ያሉ ሰዎች ተግተው ሥራቸውን እንዲሠሩና እንጀራቸውን እንዲበሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛቸዋለን፤ እንመክራቸዋለንም። 13እናንተ ግን ወንድሞች ሆይ፤ መልካም ሥራን ከመሥራት ከቶ አትታክቱ።

14በዚህ መልእክት ላይ ላለው ቃላችን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር፣ እንደዚህ ያለውን ሰው በጥንቃቄ ተከታተሉት፤ በሥራውም እንዲያፍር ከእርሱ ጋር አትተባበሩ። 15ሆኖም እንደ ወንድም ገሥጹት እንጂ እንደ ጠላት አትቍጠሩት።

የመጨረሻ ሰላምታ

16የሰላም ጌታ ራሱ በሁሉም ነገር ዘወትር ሰላም ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

17ይህን ሰላምታ በገዛ እጄ የጻፍሁት እኔ ጳውሎስ ነኝ፤ የመልእክቶቼም ሁሉ መለያ ይህ ነው፤ አጻጻፌም እንደዚህ ነው።

18የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።