历代志下 7 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 7:1-22

圣殿奉献礼

1所罗门祷告完毕,就有火从天上降下,烧尽了燔祭和其他祭物。殿里充满了耶和华的荣光, 2以致祭司不能进殿。 3全体以色列人看见有火降下,又看见耶和华的荣光停在殿上,便俯伏敬拜,称谢耶和华说:

“耶和华是美善的,

祂的慈爱永远长存。”

4所罗门王和全体民众一同向耶和华献祭。 5所罗门王献上两万二千头牛和十二万只羊,王和全体民众为上帝的殿举行奉献典礼。 6祭司在自己的岗位上侍立,利未人奏着大卫王为颂赞耶和华而为他们制造的乐器,歌颂说:“祂的慈爱永远长存。”他们对面的祭司也吹响号角,全体以色列人都肃立。

7所罗门因所造的铜坛太小,容不下燔祭、素祭和脂肪,就把耶和华殿前院子中间的地方分别出来,作圣洁之地,在那里献上燔祭和平安祭祭牲的脂肪。

8所罗门和从哈马口直至埃及小河而来的全体以色列人聚成一大群会众,一起守节期七天。 9第八天举行庄严的聚会,又举行七天献坛礼。之后,他们又欢庆七天。 10七月二十三日,所罗门王让民众各回本乡。他们看见耶和华向大卫所罗门和祂的以色列子民所施的恩惠,就满心欢喜地回家去了。

耶和华向所罗门显现

11所罗门建完了耶和华的殿和他自己的王宫,他按计划完成了耶和华殿里和他自己宫里的一切工作。 12耶和华在夜间向所罗门显现,对他说:“我已听见你的祷告,也已选择这殿作为给我献祭的地方。 13若我使天不下雨,使蝗虫吞吃地上的出产,或叫瘟疫在我民中流行, 14而这些被称为我名下的子民若谦卑下来,祈祷、寻求我的面,离开恶道,我必从天上垂听,赦免他们的罪,医治他们的土地。 15现在,我会睁眼看、留心听在这殿里献上的祷告。 16我已选择这殿,使之圣洁,永远归在我的名下,我的眼和我的心必常在那里。 17如果你像你父亲大卫一样事奉我,遵行我一切的吩咐,谨守我的律例和典章, 18我必使你的王位稳固,正如我曾与你父亲大卫立约,说,‘你的子孙必永远统治以色列。’

19“然而,如果你们背弃我指示你们的律例和诫命,去供奉、祭拜别的神明, 20我必把你们从我赐给你们的土地上铲除,并离弃我为自己的名而使之圣洁的这殿,使这殿在万民中成为笑柄、被人嘲讽。 21这殿虽然宏伟,但将来经过的人必惊讶地问,‘耶和华为什么这样对待这地方和这殿呢?’ 22人们会回答,‘因为他们背弃曾领他们祖先离开埃及的耶和华——他们的上帝,去追随、祭拜、供奉别的神明,所以耶和华把这一切灾祸降在他们身上。’”

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 7:1-22

የቤተ መቅደሱ መመረቅ

7፥1-10 ተጓ ምብ – 1ነገ 8፥62-66

1ሰሎሞን ጸሎቱን በፈጸመ ጊዜ፣ እሳት ከሰማይ ወርዶ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና ሌላውንም መሥዋዕት በላ፤ የእግዚአብሔርም ክብር ቤተ መቅደሱን ሞላው። 2የእግዚአብሔር ክብር የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ስለ ሞላው ካህናቱ ወደዚያ መግባት አልቻሉም። 3እስራኤላውያንም ሁሉ እሳቱ ሲወርድ፣ የእግዚአብሔርንም ክብር ከቤተ መቅደሱ በላይ ሲያዩ፣ በመተላለፊያው ወለል ላይ ተንበረከኩ፤ በግንባራቸውም ወደ መሬት ተደፍተው ሰገዱ፤ እንዲህ እያሉም ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀረቡ፤

“እርሱ ቸር ነውና፤

ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

እያሉም እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

4ከዚህ በኋላ ንጉሡና ሕዝቡ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት አቀረቡ። 5ንጉሥ ሰሎሞንም ሃያ ሁለት ሺሕ በሬ፣ መቶ ሃያ ሺሕ በግና ፍየል ሠዋ፤ ንጉሡና ሕዝቡም ሁሉ በዚህ ሁኔታ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቀደሱ። 6ካህናቱም እንደ ሌዋውያኑ፣ ንጉሥ ዳዊት እግዚአብሔር እንዲወደስበት የሠራውንና “ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል” በማለት እግዚአብሔርን ባመሰገነ ጊዜ፣ የተቀመጠበትን የእግዚአብሔርን የዜማ መሣሪያ ይዘው በተመደበላቸው ስፍራ ቆሙ። ካህናቱ በሌዋውያኑ ትይዩ ሆነው መለከቶቻቸውን ሲነፉም እስራኤላውያን ሁሉ ቆመው ነበር።

7ሰሎሞን የሠራው የናስ መሠዊያ የሚቃጠለውን መሥዋዕት፣ የእህሉን ቍርባንና ስቡን መያዝ ስላልቻለ፣ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ፊት ለፊት ያለውን የመካከለኛውን አደባባይ ክፍል ቀድሰው፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕቱን7፥7 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ስብ በዚያ አቃጠለ።

8በዚያን ጊዜ ሰሎሞን ከእስራኤል ሕዝብ ሁሉ ጋር ለሰባት ቀን በዓሉን አከበረ፤ ሕዝቡም ከሐማት መግቢያ እስከ ግብፅ ወንዝ ድረስ ካለው ምድር የመጣ እጅግ ታላቅ ጉባኤ ነበር። 9መሠዊያውን ለሰባት ቀን ስለ ቀደሱና የሰባት ቀን በዓል በተጨማሪ ስላከበሩ፣ በስምንተኛው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ አደረጉ። 10ሰሎሞንም በሰባተኛው ወር፣ በሃያ ሦስተኛው ቀን ወደየቤታቸው እንዲሄዱ ሕዝቡን አሰናበተ፤ ሕዝቡም እግዚአብሔር ለዳዊትና ለሰሎሞን እንዲሁም ለሕዝቡ ለእስራኤል ስላደረገው በጎ ነገር ሁሉ በልባቸው ደስ እያላቸውና ሐሤት እያደረጉ ሄዱ።

እግዚአብሔር ለሰሎሞን ተገለጠለት

7፥11-22 ተጓ ምብ – 1ነገ 9፥1-9

11ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የቤተ መንግሥቱን ሥራ ጨረሰ፤ ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና ለራሱ ቤተ መንግሥት ያደርግ ዘንድ በልቡ ያሰበውን ሁሉ ካከናወነ በኋላ፣ 12እግዚአብሔር በሌሊት ተገልጦለት እንዲህ አለው፤

“ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ ይህንም ስፍራ መሥዋዕት የሚቀርብበት ቤተ መቅደስ እንዲሆን ለራሴ መርጬዋለሁ።

13“ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማያትን በምዘጋበት ጊዜ ወይም ምድሪቱን እንዲበላ አንበጣ በማዝበት ጊዜ፣ ወይም በሕዝቤ ላይ ቸነፈር በምሰድድበት ጊዜ፣ 14በስሜ የተጠራው ሕዝቤ ራሱን አዋርዶ ቢጸልይ፣ ፊቴን ቢፈልግና ከክፉ መንገዱ ቢመለስ፣ ከሰማይ እሰማዋለሁ፤ ኀጢአቱን ይቅር እላለሁ፤ ምድሩንም እፈውሳለሁ። 15አሁንም በዚህ ስፍራ ወደሚጸለየው ጸሎት ዐይኖቼ ይገለጣሉ፤ ጆሮዎቼም ያዳምጣሉ። 16ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይህን ቤተ መቅደስ መርጫለሁ፤ ቀድሼዋለሁም። ዐይኖቼም ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ።

17“አንተም ደግሞ አባትህ ዳዊት እንዳደረገው ሁሉ በፊቴ ብትሄድ፣ ያዘዝሁህን ሁሉ ብትፈጽም፣ ሥርዐቶቼንና ሕግጋቴን ብትጠብቅ፣ 18ለአባትህ ለዳዊት፣ ‘ከዘርህ እስራኤልን የሚገዛ አታጣም’ ብዬ በገባሁለት ቃል ኪዳን መሠረት የመንግሥትህን ዙፋን አጸናለሁ።

19“እናንተ ግን እኔን ከመከተል ተመልሳችሁ የሰጠኋችሁን ሥርዐቴንና ትእዛዜን ብትተዉ፣ ሄዳችሁም ሌሎችን አማልክት ብታገለግሉና ብታመልኩ፣ 20በዚያን ጊዜ እስራኤልን ከሰጠኋቸው ምድሬ እነቅላቸዋለሁ፤ ለስሜ የቀደስሁትን ይህን ቤተ መቅደስ እተወዋለሁ፤ በሕዝቦችም ሁሉ ዘንድ መተረቻና መዘባበቻ አደርገዋለሁ። 21ይህ ቤተ መቅደስ አሁን እጅግ የሚያስደንቅ ቢሆንም በአጠገቡ የሚያልፉ ሁሉ በመገረም፤ ‘እግዚአብሔር በዚህች ምድርና በዚህ ቤተ መቅደስ ላይ እንዲህ ያለውን ነገር ያመጣው ከቶ ለምን ይሆን?’ ይላሉ፤ 22ሕዝቡም፣ ‘ይህን ሁሉ ጥፋት ያመጣባቸው፣ ከግብፅ ምድር ያወጣቸውን የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርን ትተው ሌሎችን አማልክት ስለ ተከተሉ፣ ስላመለኳቸውና ስላገለገሏቸው ነው’ ብለው ይመልሳሉ።”