历代志下 36 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 36:1-23

犹大王约哈斯

1犹大人在耶路撒冷约西亚的儿子约哈斯接替他父亲做王。 2约哈斯二十三岁登基,在耶路撒冷执政三个月。 3埃及王在耶路撒冷废掉他,并要求犹大埃及进贡三点四吨银子、三十四公斤金子。 4埃及王另立约哈斯的兄弟以利雅敬为王统治犹大耶路撒冷,给他改名为约雅敬,并把约哈斯带到埃及

犹大王约雅敬

5约雅敬二十五岁登基,在耶路撒冷执政十一年。他做他的上帝耶和华视为恶的事。 6巴比伦尼布甲尼撒起兵攻打他,用铜链把他锁着带到巴比伦7尼布甲尼撒把耶和华殿里的一些器皿带到巴比伦,放在他在巴比伦的王宫里36:7 王宫里”或译“神庙里”。8约雅敬其他的事及可憎行径和恶迹都记在以色列犹大的列王史上。他儿子约雅斤继位。

犹大王约雅斤

9约雅斤十八岁36:9 十八岁”希伯来文是“八岁”,七十士译本、叙利亚译本和列王纪下24:8是“十八岁”。登基,在耶路撒冷执政三个月零十天。他做耶和华视为恶的事。 10那年春天,尼布甲尼撒王派人把他和耶和华殿里的贵重器皿一同带到巴比伦尼布甲尼撒另立约雅斤的叔叔36:10 叔叔”参考列王纪下24:17西底迦犹大耶路撒冷的王。

犹大王西底迦

11西底迦二十一岁登基,在耶路撒冷执政十一年。 12他做他的上帝耶和华视为恶的事,耶利米先知向他传讲耶和华的话,他仍不肯在耶利米面前谦卑下来。

耶路撒冷沦陷

13尼布甲尼撒曾让他奉上帝的名起誓,他却背叛了尼布甲尼撒。他顽固不化,不肯归向以色列的上帝耶和华。 14所有祭司长和民众也都仿效外族人的一切可憎行径,犯了大罪,玷污了耶和华在耶路撒冷使之圣洁的殿。 15他们祖先的上帝耶和华因为怜爱祂的子民和祂的居所,就不断派使者来劝告他们。 16他们却嘲弄耶和华上帝的使者,藐视祂的话,嘲笑祂的先知,以致祂的愤怒临到祂的子民身上,无可挽救。

17耶和华使迦勒底人的王起兵攻打他们,在他们的圣殿里用刀击杀他们的壮丁,毫不怜悯少男少女、老人和年高者。耶和华把他们全部交在他的手中。 18上帝殿里的大小器皿,以及耶和华殿里、王宫里和众官员的所有珍宝,都被他带到巴比伦去了。 19迦勒底人焚烧上帝的殿,拆毁耶路撒冷的城墙,并且焚烧所有的宫殿,毁坏其中所有珍贵的器皿。 20没有被杀戮的人都被掳往巴比伦,做他和他子孙的奴隶,直到波斯帝国的时代。 21这就应验了耶和华借耶利米之口所说的话:这片土地享受了安息,它在荒凉中守安息,直到满了七十年。

塞鲁士王准许被掳之民返国

22波斯塞鲁士元年,耶和华为了应验祂借耶利米所说的话,就感动波斯塞鲁士,使他下诏通告全国: 23波斯塞鲁士如此说,‘天上的上帝耶和华已把天下万国都赐给我,祂吩咐我在犹大耶路撒冷为祂建造殿宇。你们当中凡属耶和华的子民,都可以去那里。愿你们的上帝耶和华与你们同在!’”

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 36:1-23

1የአገሩም ሰዎች የኢዮስያስን ልጅ ኢዮአሐዝን ወስደው በአባቱ ፈንታ በኢየሩሳሌም አነገሡት።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአሐዝ

36፥2-4 ተጓ ምብ – 2ነገ 23፥31-34

2ኢዮአሐዝ በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሃያ ሦስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሦስት ወር ገዛ። 3ከዚያም የግብፅ ንጉሥ በኢየሩሳሌም ካለው ዙፋኑ አወረደው፣ በአገሩም ላይ አንድ መቶ መክሊት36፥3 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብርና አንድ መክሊት36፥3 34 ኪሎ ግራም ይህል ነው። ወርቅ ግብር ጣለበት። 4የግብፅም ንጉሥ የኢዮአሐዝን ወንድም ኤልያቄምን በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ አነገሠው፤ ስሙንም ለውጦ ኢዮአቄም አለው። ኒካዑም የኤልያቄምን ወንድም ኢዮአሐዝን ይዞ ወደ ግብፅ ወሰደው።

የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም

36፥5-8 ተጓ ምብ – 2ነገ 23፥36–24፥6

5ኢዮአቄም በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሃያ አምስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ አንድ ዓመት ገዛ። በአምላኩም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ። 6የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በእርሱ ላይ ዘመተ፤ ወደ ባቢሎንም ይወስደው ዘንድ በናስ ሰንሰለት አሰረው። 7እንደዚሁም ናቡከደነፆር የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ዕቃ ወስዶ፣ ባቢሎን ባለው በራሱ ቤተ ጣዖት36፥7 ወይም ቤተ መንግሥት ተብሎ መተርጐም ይችላል። አኖረው።

8በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ተግባሩ የፈጸመው አስጸያፊ ድርጊትና በእርሱ ላይ የተገኘበት ሁሉ በእስራኤልና በይሁዳ ነገሥታት መጽሐፍ ተጽፏል። ልጁ ዮአኪንም በእርሱ ፈንታ ነገሠ።

የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን

36፥9-10 ተጓ ምብ – 2ነገ 24፥8-17

9ዮአኪን በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ዐሥራ ስምንት36፥9 አንድ የዕብራይስጥ ቅጅ ጥቂት የሰብዓ ሊቃናትና የሱርስት ትርጕሞች (እንዲሁም 2ነገ 24፥8) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን ስምንት ይላሉ። ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሦስት ወር ከዐሥር ቀን ገዛ፤ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ። 10በጸደይም ወራት ንጉሡ ናቡከደነፆር ልኮ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ ካላቸው ዕቃዎች ጋር ወደ ባቢሎን ወሰደው። የዮአኪንንም አጎት36፥10 ዕብራይስጡ ወንድም ይላል (እንዲሁም 2ነገ 24፥17 ይመ)። ሴዴቅያስን በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ አነገሠው።

የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ

36፥11-16 ተጓ ምብ – 2ነገ 24፥18ኤር 52፥1-3

11ሴዴቅያስ በነገሠ ጊዜ፣ ዕድሜው ሃያ አንድ ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ አንድ ዓመት ገዛ። 12እርሱም በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸመ፤ የእግዚአብሔርን ቃል በተናገረው በነቢዩ በኤርምያስ ፊትም ራሱን ዝቅ አላደረገም። 13እንደዚሁም በእግዚአብሔር ስም አምሎት በነበረው በንጉሥ ናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ፤ ዐንገቱን አደነደነ፤ ልቡንም አጠነከረ እንጂ ወደ እስራኤል አምላክ ወደ እግዚአብሔር አልተመለሰም። 14ከዚህም ላይ የካህናቱና የሕዝቡ መሪዎች ሁሉ፣ አስጸያፊ የሆኑትን የአሕዛብን ልማዶች በመከተልና በኢየሩሳሌም የተቀደሰውን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በማርከስ፣ ባለ መታመናቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሱ ሄዱ።

የኢየሩሳሌም መውደቅ

36፥17-20 ተጓ ምብ – 2ነገ 25፥1-21ኤር 52፥4-27

36፥22-23 ተጓ ምብ – ዕዝ 1፥1-3

15የአባቶቻቸው አምላክ እግዚአብሔር ለሕዝቡና ለማደሪያው ስለ ዐዘነ፣ መልእክተኞቹን ይልክ ነበር፤ 16እነርሱ ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ እስኪነሣሣና ፈውስም እስከማይገኝላቸው ድረስ በእግዚአብሔር መልእክተኞች ላይ ተሣለቁ፤ ቃሉን ናቁ፤ ነቢያቱንም አቃለሉ። 17ስለዚህ የባቢሎናውያንን36፥17 ወይም ከለዳውያን ንጉሥ አመጣባቸው፤ እርሱም ወጣቶቻቸውን በቤተ መቅደሱ ውስጥ በሰይፍ ፈጀ፤ ወጣቱንም ሆነ ወጣቲቱን፣ ሽማግሌውንም ሆነ በዕድሜ የገፋውን አላስቀረም፤ እግዚአብሔር ሁሉንም ለናቡከደነፆር አሳልፎ ሰጠው። 18እርሱም ትልልቁንም ሆነ ትንንሹን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ዕቃ በሙሉ፣ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሀብት፣ የንጉሡንና የሹማምቱን ሀብት ሁሉ ወደ ባቢሎን አጋዘ። 19የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በእሳት አቃጠሉ፤ የኢየሩሳሌምን ቅጥሮች አፈረሱ፤ ቤተ መንግሥቶቹን በሙሉ አቃጠሉ፤ በዚያ የነበረውንም የከበረ ዕቃ በሙሉ አጠፉ። 20ከሰይፍ የተረፉትን ቅሬታዎች በምርኮ ወደ ባቢሎን ወሰዳቸው፤ እስከ ፋርስ መንግሥት መነሣትም ድረስ የእርሱና የልጆቹ አገልጋዮች ሆኑ። 21ምድሪቱም የሰንበት ዕረፍት አገኘች፤ በኤርምያስ የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ፣ ሰባው ዓመት እስኪያበቃ ድረስ፣ ባድማ በነበረችበት ዘመን ሁሉ ዐረፈች።

22በኤርምያስ የተነገረው የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ፣ በፋርስ ንጉሥ በቂሮስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ዓመት፣ በግዛቱ ሁሉ ዐዋጅ እንዲያስነግርና ይህም እንዲጻፍ እግዚአብሔር የፋርስን ንጉሥ የቂሮስን መንፈስ አነሣሣ፤ እርሱም እንዲህ አለ፤

23“የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ እንዲህ ይላል፤

“ ‘የሰማይ አምላክ እግዚአብሔር የምድርን መንግሥታት ሁሉ ሰጥቶኛል፤ በይሁዳ በምትገኘው በኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ እሠራለት ዘንድ አዝዞኛል፤ ከሕዝቡ በመካከላችሁ የሚገኝ ማናቸውም ሰው፣ እግዚአብሔር አምላኩ ከእርሱ ጋር ይሁን፤ እርሱም ወደዚያው ይውጣ።’ ”