历代志下 13 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 13:1-22

亚比雅与耶罗波安争战

1耶罗波安王执政第十八年,亚比雅登基做犹大王, 2耶路撒冷执政三年。他母亲叫米该亚13:2 米该亚”在代下11:20是“押沙龙的女儿玛迦”。,是基比亚乌列的女儿。亚比雅耶罗波安之间常有争战。 3有一次,亚比雅率领四十万精兵出战,耶罗波安率领八十万精兵列阵迎战。

4亚比雅站在以法莲山区的西玛莲山上说:“耶罗波安和全体以色列人啊,你们听我说, 5你们不知道以色列的上帝耶和华曾经立下永世之约13:5 永世之约”希伯来文是“盐约”。,要把以色列国永远赐给大卫和他的子孙吗? 6尼八的儿子耶罗波安本是大卫的儿子所罗门的仆人,他却背叛他的主人, 7召集一群无赖恶棍,与所罗门的儿子罗波安作对。那时,罗波安年轻怯懦,无力抵抗。

8“现在你们仗着人多势众,又有耶罗波安制造的金牛犊作为你们的神明,便企图反抗大卫子孙所治理的耶和华的国度。 9你们赶走了做耶和华祭司的亚伦之后裔和利未人,效法外族人的恶俗为自己设立祭司。任何人牵来一头公牛犊和七只公绵羊,就可以自封为假神的祭司。

10“至于我们,耶和华是我们的上帝,我们没有背弃祂,我们有亚伦的后裔做祭司事奉耶和华,也有利未人各尽其职。 11他们每天早晚向耶和华献燔祭,烧芬芳的香,把供饼摆在洁净13:11 洁净”指宗教礼仪上的洁净。的桌子上,每晚点上金灯台的灯。我们遵守我们上帝耶和华的吩咐,你们却背弃祂。 12上帝与我们同在,祂率领我们。祂的祭司就要吹响向你们进攻的号角。以色列人啊,不要与你们祖先的上帝耶和华作对,因为你们绝不会得胜。”

13耶罗波安却在犹大人后面设伏兵,企图前后夹攻他们。 14犹大人转身,发现自己前后受敌,就呼求耶和华。祭司吹响号角, 15犹大人便吶喊,上帝使耶罗波安以色列人败在亚比雅犹大人面前。 16以色列人从犹大人面前逃跑,上帝把他们交在犹大人手中。 17亚比雅和他的军队大败以色列人,歼灭了他们五十万精兵。 18这样,以色列人被击败,犹大人因为倚靠他们祖先的上帝耶和华而大获全胜。

19亚比雅追赶耶罗波安,攻取了伯特利耶沙拿以法拉音各城以及它们周围的村庄。 20亚比雅在世之日,耶罗波安再也没有恢复势力。后来,耶和华攻击他,他就死了。 21亚比雅却日渐强大,他有十四个妻妾、二十二个儿子、十六个女儿。 22亚比雅其余的事及其言行都记在易多先知的史记上。

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 13:1-22

የይሁዳ ንጉሥ አብያ

13፥1-2፡22–14፥1 ተጓ ምብ – 1ነገ 15፥1-26-8

1ኢዮርብዓም በነገሠ በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት፣ አብያ በይሁዳ ነገሠ። 2በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሦስት ዓመት ገዛ። እናቱ ሚካያ13፥2 ብዙ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም 2ዜና 11፥20 እና 1ነገ 15፥2) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ሚካያ ይላል። ትባላለች፤ እርሷም የገብዓ ተወላጅ የኡርኤል ልጅ ነበረች።

በአብያና በኢዮርብዓምም መካከል ጦርነት ነበር። 3አብያ አራት መቶ ሺሕ ብርቱ ተዋጊዎች ይዞ ዘመተ፤ ኢዮርብዓምም ስምንት መቶ ሺሕ ብርቱ ተዋጊዎች ይዞ በመውጣት ጠበቀው።

4አብያ በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በጽማራይም ተራራ ላይ ቆሞ፣ እንዲህ አለ፤ “ኢዮርብዓምና እስራኤል ሁሉ አድምጡኝ! 5የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ዳዊትና ዘሮቹ በእስራኤል ላይ ለዘላለም እንዲነግሡ በጨው ኪዳን የሰጣቸው መሆኑን አታውቁምን? 6የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ባሪያ የነበረው የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም ግን በጌታው ላይ ዐመፀ። 7የሰሎሞን ልጅ ሮብዓም ገና ሕፃን ሳለ፣ ምንም ማድረግ በማይችልበትና እነርሱንም ለመቋቋም ዐቅሙ በማይፈቅድለት ጊዜ የማይረቡ ጥቂት ወሮበሎች በዙሪያው ተሰበሰቡበት፣ በረቱበትም።

8“አሁንም እናንተ በዳዊት ዘርዐ ትውልድ እጅ ያለውን የእግዚአብሔርን መንግሥት ልትቋቋሙ አስባችኋል። በርግጥም በሰራዊት ረገድ እጅግ ብዙ ናችሁ፤ አማልክታችሁ ይሆኑ ዘንድ ኢዮርብዓም የሠራቸውንም የወርቅ ጥጆች ይዛችኋል። 9ደግሞስ የአሮን ልጆች የሆኑትን የእግዚአብሔርንካህናትና ሌዋውያንን አባርራችሁ፣ ሌሎች ሕዝቦች እንደሚያደርጉት ሁሉ፣ እናንተም የራሳችሁን ካህናት አልሾማችሁምን? አንድ ኮርማና ሰባት አውራ በግ ይዞ ራሱን ለመቀደስ የሚመጣ ማናቸውም ሰው አማልክት ላልሆኑ ለእነዚያ ጣዖታት ካህን ይሆናል።

10“ለእኛ ግን አምላካችን እግዚአብሔር ነው፤ እርሱንም አልተውንም፤ እግዚአብሔርን በማገልገል ላይ ያሉት ካህናት የአሮን ልጆች ሲሆኑ፣ ረዳቶቻቸውም ሌዋውያኑ ናቸው። 11እነርሱም በየጧቱና በየማታው የሚቃጠል መሥዋዕትና ሽታው ደስ የሚያሰኝ ዕጣን ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፤ የገጹን ኅብስት በሥርዐቱ መሠረት በነጻው ጠረጴዛ ላይ ያኖራሉ፤ በየማታውም በወርቁ መቅረዝ ላይ ያሉትን ቀንዲሎች ያበራሉ፤ እኛም የአምላካችንን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንፈጽማለን፤ እናንተ ግን ትታችሁታል። 12እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ መሪያችንም እርሱ ነው። መለከት የያዙ ካህናቱም የጦርነቱን ድምፅ በእናንተ ላይ ያሰማሉ። እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፤ አይቀናችሁምና፣ ከአባቶቻችሁ አምላክ ከእግዚአብሔር ጋር አትዋጉ።”

13በዚህ ጊዜ ኢዮርብዓም ከሰራዊቱ ከፊሉን ከይሁዳ ሰራዊት በስተ ጀርባ እንዲያደፍጡ ላከ፤ የቀረውም ሰራዊት ከእርሱ ጋር የይሁዳን ሰራዊት ፊት ለፊት እንዲገጥሙ አደረገ። 14የይሁዳም ሰዎች ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከፊትና ከኋላ መከበባቸውን አዩ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጮኹ፤ ካህናቱም መለከታቸውን ነፉ። 15የይሁዳም ሰዎች በፉከራ የጦርነት ድምፅ አሰሙ፤ እግዚአብሔር ኢዮርብዓምንና እስራኤልን ሁሉ በአብያና በይሁዳ ፊት ፊጽሞ መታቸው። 16እስራኤላውያን ከይሁዳ ፊት ሸሹ፤ እግዚአብሔርም በእጃቸው አሳልፎ ሰጣቸው። 17አብያና ሰዎቹም ከባድ ጕዳት አደረሱባቸው፤ ከዚህ የተነሣም ከእስራኤል ብርቱ ተዋጊዎች መካከል አምስት መቶ ሺሕ ሰዎች ተገደሉ። 18በጦርነቱም የእስራኤል ሰዎች ተዋረዱ፣ የይሁዳ ሰዎች ግን በአባቶቻቸው አምላክ በእግዚአብሔር ታምነዋልና ድል ነሡ።

19አብያም ኢዮርብዓምን አሳድዶ የቤቴልን፣ የይሻናንና የዔፍሮንን ከተሞች ከነ መንደሮቻቸው ወሰደበት። 20ኢዮርብዓም በአብያ ዘመን እንደ ገና ሊያንሠራራ አልቻለም፤ ከዚያም እግዚአብሔር ስለ ቀሠፈው ሞተ።

21አብያ ግን ይበልጥ እየበረታ ሄደ፤ ዐሥራ አራት ሚስቶች አግብቶም ሃያ ሁለት ወንዶችና ዐሥራ ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት።

22በአብያ ዘመን የተከናወነው ተግባር፣ እርሱ የፈጸመውና የተናገረው ሁሉ በነቢዩ በአዶ የታሪክ መዛግብት ተጽፏል።