历代志上 5 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志上 5:1-26

吕便的后裔

1以色列的长子原是吕便,但因为他玷污了父亲的床5:1 指跟父亲的妾通奸一事,参见创世记35:22,他长子的名分就给了他弟弟约瑟的后代。因此,按家谱他不是长子。 2犹大虽然在众弟兄中最强大,君王也是出自他的后裔,长子的名分却属于约瑟3以色列长子吕便的儿子是哈诺法路希斯伦迦米4约珥的儿子是示玛雅示玛雅的儿子是歌革歌革的儿子是示每5示每的儿子是米迦米迦的儿子是利·亚雅利·亚雅的儿子是巴力6巴力的儿子是备·拉备·拉吕便支派的首领,被亚述提革拉·毗尼色掳去。 7按家谱记载,他做族长的亲族是耶利撒迦利雅比拉8比拉亚撒的儿子,亚撒示玛的儿子,示玛约珥的儿子。约珥住在亚罗珥尼波巴力·免一带。 9他们的牲畜在基列繁殖众多,便又向东迁移到幼发拉底河西边的旷野。 10扫罗执政期间,吕便人与夏甲人交战,打败了夏甲人,占领了基列东边的整片土地。

迦得的后裔

11迦得的后代住在毗邻吕便支派的巴珊,向东远至撒迦12巴珊做首领的有族长约珥、副族长沙番以及雅乃沙法13他们同族的弟兄有米迦勒米书兰示巴约赖雅干细亚希伯,共七人。 14这些都是亚比孩的儿子。亚比孩户利的儿子,户利耶罗亚的儿子,耶罗亚基列的儿子,基列米迦勒的儿子,米迦勒耶示筛的儿子,耶示筛耶哈多的儿子,耶哈多布斯的儿子。 15古尼的孙子、押比碟的儿子亚希是他们家族的族长。 16他们住在基列巴珊巴珊附近的乡村以及沙仑所有的草原,直到四围的边界地带。 17这些人是在犹大约坦以色列耶罗波安执政期间被记录在族谱里的。

18吕便支派、迦得支派和玛拿西半个支派中善用盾牌、刀剑、弓箭、能征善战的勇士共有四万四千七百六十人。 19他们与夏甲人、伊突人、拿非施人和挪答人打仗, 20击败了夏甲人及其盟军,因为他们信靠上帝,在作战的时候向上帝求助,上帝应允了他们的祈求。 21他们从敌人那里掳走了五万只骆驼、二十五万只羊、两千头驴和十万人口。 22敌人伤亡惨重,因为他们有上帝的帮助。他们占据敌人的土地,一直到被掳的时候。

玛拿西的半个支派

23玛拿西半个支派的人住在从巴珊巴力·黑们示尼珥黑门山一带。 24他们的族长以弗以示以列亚斯列耶利米何达威雅雅叠都是英勇的战士,是著名的人物和各家族的首领。

25可是,他们却背弃他们祖先的上帝,与当地居民的神明苟合。上帝曾在他们面前毁灭那些居民。 26因此,以色列的上帝驱使亚述普勒,即提革拉·毗尼色,把吕便人、迦得人、玛拿西半个支派的人掳到哈腊哈博哈拉歌散河边,他们至今还在那里。

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 5:1-26

ሮቤል

1የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ልጆች፤ ሮቤል የበኵር ልጅ ቢሆንም፣ የአባቱን መኝታ ስላረከሰ፣ የብኵርና መብቱ ለእስራኤል ልጅ ለዮሴፍ ልጆች ተሰጥቷል። ከዚህም የተነሣ ትውልዱ የበኵርነቱን ተራ ይዞ ሊቈጠር አልቻለም። 2ይሁዳ ከወንድሞቹ ይልቅ ብርቱ ነበረ፤ ገዥ የወጣው ከእርሱ ቢሆንም፣ የብኵርና መብቱ የተላለፈው ለዮሴፍ ነበረ። 3የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ወንዶች ልጆች፤

ሄኖኅ፣ ፋሉሶ፣ አስሮን፣ ከርሚ።

4የኢዩኤል ዘሮች፤

ልጁ ሸማያ፣ ልጁ ጎግ፣

ልጁ ሰሜኢ፣ 5ልጁ ሚካ፣

ልጁ ራያ፣ ልጁ ቢኤል፣

6የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር ማርኮ የወሰደው ልጁ ብኤራ።

7የቤተ ሰቡ የዘር ትውልድ በየጐሣ በየጐሣው ሲቈጠር እንደሚከተለው ነው፤

የጐሣ አለቃ የሆነው ኢዮኤል፣ ዘካርያስ፣ 8የኢዮኤል ልጅ፣ የሽማዕ ልጅ፣ የዖዛዝ ልጅ ቤላ፣ እነዚህ ከአሮዔር እስከ ናባውና እስከ በኣልሜዎን ድረስ በሚገኘው ምድር ላይ ሰፈሩ። 9ከብቶቻቸው በገለዓድ ምድር በዝተው ስለ ነበር፣ በምሥራቅ በኩል ወደ ኤፍራጥስ ወንዝ እስከ ምድረ በዳው ዳርቻ ድረስ የሚገኘውን ምድር ያዙ።

10በሳኦልም ዘመነ መንግሥት በእጃቸው ተመትተው ድል ከተደረጉት አጋራውያን ጋር ተዋጉ፤ በመላው የገለዓድ ምሥራቃዊ ክፍል የሚገኙትን መኖሪያዎቻቸውን ያዙ።

ጋድ

11የጋድ ነገድ ደግሞ ከእነርሱ ቀጥሎ እስከ ሰልካ ድረስ በሚገኘው በባሳን ምድር ኖሩ፤

12አለቃው ኢዮኤል፣ ሁለተኛው ሳፋም ከዚያም ያናይና ሰፋጥ ሆነው በባሳን ተቀመጡ።

13ቤተ ዘመዶቻቸውም በየቤተ ሰቡ እነዚህ ነበሩ፤

ሚካኤል፣ ሜሱላም፣ ሳባ፣ ዮራይ፣ ያካን፣ ዙኤ፣ ኦቤድ፤ በአጠቃላይ ሰባት ነበሩ።

14እነዚህ ደግሞ የቡዝ ልጅ፣ የዬዳይ ልጅ፣ የኢዬሳይ ልጅ፣ የሚካኤል ልጅ፣ የገለዓድ ልጅ፣ የኢዳይ ልጅ፣ የዑሪ ልጅ፣ የሑሪ ልጅ፣ የአቢካኢል ልጆች ናቸው።

15የቤተ ሰባቸውም አለቃ የጉኒ ልጅ፣ የአብዲኤል ልጅ አሒ ነበረ።

16ጋዳውያንም በገለዓድ፣ በባሳንና እስከ ዳርቻዋ በሚገኙት መንደሮች እንዲሁም በሳሮን በሚገኙ የግጦሽ ስፍራዎች ሁሉና ከዚያም ወዲያ ዐልፈው ተቀመጡ።

17እነዚህ ሁሉ በትውልድ መዝገብ የሰፈሩት በይሁዳ ንጉሥ በኢዮአታምና በእስራኤል ንጉሥ በኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት ነው።

18የሮቤል፣ የጋድና የምናሴ ነገድ እኩሌታ አርባ አራት ሺሕ ሰባት መቶ ስድሳ ብቁ የጦር ሰዎች ነበሯቸው። እነርሱም ጋሻ መያዝ፣ ሰይፍ መምዘዝና ቀስት መሳብ የሚችሉ ጠንካራና በውጊያ የሠለጠኑ ናቸው። 19እነዚህም በአጋራውያን፣ በኢጡር፣ በናፌስ፣ በናዳብ ላይ ዘመቱ። 20በጦርነቱም ላይ ወደ እግዚአብሔር ጮኸው ስለ ነበር፣ በውጊያው ረዳቸው፤ አጋራውያንንና የጦር አጋሮቻቸውን ሁሉ አሳልፎ ሰጣቸው፤ ስለ ታመኑበትም ጸሎታቸውን ሰማ። 21የአጋራውያንንም እንስሶች ማረኩ፤ እነዚህም አምሳ ሺሕ ግመሎች፣ ሁለት መቶ አምሳ ሺሕ በጎችና ሁለት ሺሕ አህዮች ነበሩ። እንዲሁም አንድ መቶ ሺሕ ሰው ማረኩ። 22ውጊያው የእግዚአብሔር ስለ ነበር፣ ሌሎችም ብዙ ሰዎች ተገደሉ። እስከ ምርኮ ጊዜ ድረስ ምድሪቱ በእጃቸው ነበረች።

እኩሌታው የምናሴ ነገድ

23የምናሴ ነገድ እኩሌታ ሕዝብ ቍጥር ብዙ ነበረ፤ እነርሱም ከባሳን ጀምሮ እስከ በኣልአርሞንዔም ድረስ ባለው ምድር ሰፈሩ፤ ይህም እስከ ሳኔር አርሞንዔም ተራራ ድረስ ማለት ነው።

24የየቤተ ሰቡም አለቆች እነዚህ ነበሩ፤ ዔፌር፤ ይሽዒ፣ ኤሊኤል፣ ዓዝርኤል፣ ኤርምያ፣ ሆዳይዋ፣ ኢየድኤል፤ እነዚህ ጀግና ተዋጊዎች፣ የታወቁ ሰዎችና የየቤተ ሰባቸው አለቆች ነበሩ። 25ይሁን እንጂ ለአባቶቻቸው አምላክ ታማኞች አልሆኑም፤ እግዚአብሔር ከፊታቸው ያጠፋቸውን የምድሪቱን አሕዛብ አማልክት በማምለክ አመነዘሩ። 26ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የአሦርን ንጉሥ የፎሐን መንፈስ ይኸውም የቴልጌልቴልፌልሶርን መንፈስ አነሣሥቶ የሮቤልን፣ የጋድንና፣ የምናሴን ነገድ እኩሌታ ማርኮ እንዲወስድ አደረገ። እነዚህንም ወደ አላሔ፣ ወደ አቦር፣ ወደ ሃራና ወደ ጎዛን ወንዝ ዳርቻ አፈለሳቸው፤ እነርሱም እስከ ዛሬ ድረስ በዚያ ይገኛሉ።