创世记 13 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

创世记 13:1-18

亚伯兰与罗得分道扬镳

1亚伯兰带着妻子、侄儿罗得和所有的一切离开埃及去南地。 2这时候亚伯兰已经拥有很多牲畜和金银。 3-4他从南地渐渐迁移到伯特利,到了他从前在伯特利中间搭帐篷和筑坛的地方。他又在那里求告耶和华。 5亚伯兰同行的罗得也有牛群、羊群和帐篷。 6他们的牲畜很多,那地方容纳不下,他们无法住在一起。 7亚伯兰的牧人和罗得的牧人彼此争执。那时,迦南人和比利洗人也住在那里。

8亚伯兰罗得说:“我们不该彼此争执,我们的牧人也不该互相争执,因为我们是骨肉至亲。 9整片土地不就在你面前吗?我们分开吧。如果你往左边去,我就往右边走;如果你往右边去,我就往左边走。” 10罗得举目眺望,看见整个约旦河平原,远至琐珥,水源充足。在耶和华还没有毁灭所多玛蛾摩拉之前,那地方就好像耶和华的伊甸园,又像埃及11于是,罗得选了整个约旦河平原,向东迁移,他们便分开了。 12亚伯兰住在迦南罗得则住在平原的城邑里,并渐渐把帐篷迁移到所多玛附近。 13所多玛人极其邪恶,在耶和华眼中罪恶滔天。

14罗得离开后,耶和华对亚伯兰说:“从你站的地方向东西南北眺望, 15你所能看见的地方,我都要赐给你和你的后代,直到永远。 16我要使你的后代多如地上的尘土,人若能数算地上的尘土,才能数算你的后代。 17你起来走遍这片土地,因为我要把这片土地赐给你。” 18亚伯兰就把帐篷迁移到希伯仑幔利的橡树那里居住,在那里为耶和华筑了一座祭坛。

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 13:1-18

የአብራምና የሎጥ መለያየት

1አብራም ሚስቱንና ንብረቱን ሁሉ ይዞ ከግብፅ ወደ ኔጌብ ሄደ፤ ሎጥም አብሮት ነበረ። 2አብራም በከብት፣ በብርና በወርቅ እጅግ በልጽጎ ነበር።

3አብራም ከኔጌብ ተነሥቶ እስከ ቤቴል ተጓዘ፤ ቀድሞ በቤቴልና በጋይ መካከል ድንኳኑን ከተከለበት፣ 4ለመጀመሪያ ጊዜም መሠዊያ ካቆመበት ስፍራ ደረሰ፤ በዚያም የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም ጠራ።

5ከአብራም ጋር አብሮት ይጓዝ የነበረው ሎጥ በጎች፣ ከብቶችና ድንኳኖች ነበሩት። 6ሆኖም ሁለቱ አንድ ላይ ሲኖሩ ስፍራው አልበቃቸውም፤ ንብረታቸው እጅግ ብዙ ስለ ነበር፣ አብረው መኖር አልቻሉም። 7ይህም በመሆኑ በአብራምና በሎጥ እረኞች መካከል ጠብ ተፈጠረ። በዚያን ዘመን ከነዓናውያንና ፌርዛውያን በዚያው አገር ይኖሩ ነበር።

8አብራምም ሎጥን እንዲህ አለው፤ “እኛ ወንድማማቾች ነንና፣ በአንተና በእኔ ወይም በእረኞቻችን መካከል ጠብ ሊኖር አይገባም። 9ይኸው እንደምታየው አገሩ ሰፊ ነው፤ ብንለያይ ይሻላል። አንተ ግራውን ብትመርጥ፣ እኔ ወደ ቀኝ እሄዳለሁ፤ አንተ ቀኙን ብትመርጥ፣ እኔ ወደ ግራ አመራለሁ።”

10ሎጥ ዐይኑን አቅንቶ ሲመለከት፣ የዮርዳኖስ ረባዳ ሜዳ እንደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ገነት፣ በዞዓር አቅጣጫ እንዳለው እንደ ግብፅ ምድር ውሃማ ቦታ ሆኖ አገኘው። እንዲህም የነበረው እግዚአብሔር (ያህዌ) የሰዶምንና የገሞራን ከተሞች ከማጥፋቱ በፊት ነው። 11ሎጥ የዮርዳኖስን ረባዳ ሜዳ በሙሉ መርጦ ወደ ምሥራቅ አመራ፤ ሁለቱ ሰዎች በዚሁ ተለያዩ። 12አብራም መኖሪያውን በከነዓን ምድር አደረገ፤ ሎጥ ግን በረባዳው ሜዳ ውስጥ ባሉት ከተሞች መካከል በሰዶም አቅራቢያ ድንኳኑን ተከለ። 13የሰዶም ሰዎች ግን ክፉዎችና በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እጅግ ኀጥኣን ነበሩ።

14ሎጥ ከተለየው በኋላ እግዚአብሔር (ያህዌ) አብራምን እንዲህ አለው፤ “ካለህበት ስፍራ ቀና ብለህ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ፣ ወደ ምሥራቅና ወደ ምዕራብ ተመልከት፤ 15ዐይንህ የሚያየውን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘርህ ለዘላለም እሰጣለሁ። 16ዘርህን እንደ ምድር ትቢያ አበዛዋለሁ፤ ማንም የምድርን ትቢያ ሊቈጥር እንደማይችል ሁሉ የአንተም ዘር የማይቈጠር ይሆናል። 17እንግዲህ ምድሪቱን ስለምሰጥህ ተነሣ፤ በርዝመቷም፣ በስፋቷም ተመላለስባት።”

18አብራምም ድንኳኑን ነቀለ፤ ሄዶም ኬብሮን በሚገኙት ትልልቅ የመምሬ ዛፎች አጠገብ ተቀመጠ፤ በዚያም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሠዊያ ሠራ።