列王纪下 25 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪下 25:1-30

1西底迦执政第九年十月十日,巴比伦尼布甲尼撒率领全军攻打耶路撒冷,在城外安营,修筑围城的高台。 2城一直被围困到西底迦执政第十一年。 3那年四月九日,城里饥荒非常严重,百姓无粮可吃。 4城被攻破,城里的所有士兵便在夜间穿过御花园,从两城墙中间的门逃往亚拉巴。当时迦勒底人仍四面包围着城。 5迦勒底军队追赶西底迦,在耶利哥平原追上了他,他的军队都四散而逃。 6迦勒底人擒住西底迦,把他押到利比拉巴比伦王,在那里审判他。 7巴比伦王在西底迦面前杀了他的众子,又剜去他的双眼,把他用铜链锁着押往巴比伦

圣殿被毁

8巴比伦尼布甲尼撒执政第十九年五月七日,他的臣仆——护卫长尼布撒拉旦来到耶路撒冷9放火焚烧耶和华的殿、王宫及城内所有的房屋。他烧毁了所有重要建筑。 10他率领的迦勒底军队拆毁了耶路撒冷四围的城墙。 11护卫长尼布撒拉旦掳去城里剩下的百姓、投降巴比伦王的人以及其他人, 12只留下一些最贫穷的人,让他们照料葡萄园、耕种田地。

13迦勒底人打碎耶和华殿中的铜柱、盆座和铜海,把铜运往巴比伦14并带走了盆、铲、蜡剪、碟子及一切献祭用的铜器。 15护卫长还带走了火鼎、碗等一切金银器具。

16所罗门为耶和华的殿所造的两根铜柱、一个铜海和一些盆座,用的铜多得无法计算。 17铜柱高八米,柱顶有柱冠,高一点三五米。柱冠周围装饰着铜网和铜石榴。两根柱子都一样。

18护卫长尼布撒拉旦掳走祭司长西莱雅、副祭司长西番亚和三名殿门守卫, 19还从城中拿住一名统管士兵的将领、王的五个亲信、一名负责招兵的书记和六十名平民。 20护卫长尼布撒拉旦把他们带到利比拉去见巴比伦王, 21巴比伦王在那里处死了他们。犹大人就这样被掳去,离开了家园。

基大利做犹大省长

22巴比伦尼布甲尼撒任命基大利治理犹大的余民。基大利沙番的孙子、亚希甘的儿子。 23犹大众将领和他们的下属听到巴比伦王委任基大利治理犹大的消息后,便都到米斯巴基大利。他们是尼探雅的儿子以实玛利加利亚的儿子约哈难尼陀法单户篾的儿子西莱雅玛迦雅撒尼亚24基大利向他们和他们的下属发誓,说:“你们不用害怕那些迦勒底官员。你们住在这地方服侍巴比伦王,就会平安无事。” 25七月,王室后裔以利沙玛的孙子、尼探雅的儿子以实玛利带着十个人在米斯巴刺杀了基大利以及跟他一起的犹大人和迦勒底人。 26因为害怕迦勒底人报复,犹大众人不论贵贱,都和众将领一起逃往埃及

约雅斤获释

27巴比伦以未·米罗达在他执政的元年十二月二十七日,即犹大约雅斤被掳后第三十七年,施恩释放了约雅斤28并好言相待,使他的地位高过被掳到巴比伦的其他各王。 29约雅斤脱去了囚衣,终生与巴比伦王一起吃饭。 30在他有生之年,巴比伦王供应他每天的需用。

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 25:1-30

1በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት በዘጠነኛው ዓመት በዐሥረኛው ወር፣ ከወሩም በዐሥረኛው ቀን የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር መላ ሰራዊቱን ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ዘመተ፤ ከከተማዪቱ ቅጥር ውጭ ሰፈረ፤ ዙሪያውንም በሙሉ በዕርድ ከበባት። 2ከተማዪቱም እስከ ሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት ዐሥራ አንደኛ ዓመት ድረስ እንዲሁ እንደ ተከበበች ቈየች።

3በአራተኛው25፥3 ኤር 52፥6 ይመ ወር በዘጠነኛው ቀን በከተማዪቱ ውስጥ የተከሠተው ራብ ጸንቶ ስለ ነበር ሕዝቡ የሚቀምሰው ዐጣ። 4ምንም እንኳ ባቢሎናውያን25፥4 በዚህና በቍጥር 13፡25 እንዲሁም 26 ላይ፣ ከለዳውያን ከተማዪቱን እንደ ከበቧት ቢሆንም የከተማዪቱ ቅጥር ተጣሰ፤ ሰራዊቱም ሁሉ በንጉሡ አትክልት አጠገብ ባሉት በሁለቱ ቅጥሮች መካከል በሚገኘው በር ዐልፎ በሌሊት ሸሸ፤ ሽሽቱም ወደ ዮርዳኖስ ሸለቆ25፥4 ወይም፣ በዓረባም ነበር። 5ይሁን እንጂ የባቢሎን25፥5 በዚህም ሆነ በቍጥር 10 እና 24 ላይ፣ ከለዳውያን ሰራዊት ንጉሡን ተከታትሎ በኢያሪኮ ሜዳ ላይ ደረሰበት። ወታደሮቹ ሁሉ ተለይተውት ተበታትነው ነበር። 6እርሱም ተያዘ፤ በዚያን ጊዜ ሪብላ ወደ ነበረው ወደ ባቢሎን ንጉሥ አመጡት፤ ፈረዱበትም። 7ሴዴቅያስ ዐይኑ እያየም የገዛ ልጆቹን ገደሉበት፤ ከዚያም ሁለት ዐይኖቹን በማውጣት በናስ ሰንሰለት አስረው ወደ ባቢሎን ወሰዱት።

8የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በነገሠ በዐሥራ ዘጠነኛው ዓመት፣ በአምስተኛው ወር ከወሩም በሰባተኛው ቀን የክብር ዘቡ ሰራዊት አዛዥና የባቢሎን ንጉሥ ከፍተኛ ባለ ሥልጣን የሆነው ናቡዘረዳን ወደ ኢየሩሳሌም መጣ። 9የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ፣ ቤተ መንግሥቱንና በኢየሩሳሌም የሚገኙትን ቤቶች ሁሉ አቃጠለ፤ እያንዳንዱንም ታላላቅ ሕንጻ ለእሳት ዳረገው። 10በክብር ዘቡ አዛዥ የተመራው መላው የባቢሎን ሰራዊትም በኢየሩሳሌም ዙሪያ የነበረውን ቅጥር አፈረሰው። 11የክብር ዘቡ አዛዥም በከተማዪቱ ቀርቶ የነበረውን፣ ከድቶም በዚያ የተገኘውን ሰው ሁሉ ወደ ባቢሎን ንጉሥ የገባውን ጭምር በምርኮ ወደ ባቢሎን ወሰደው። 12ሆኖም አዛዡ ከአገሬው ሰዎች ምንም የሌላቸውን ድኾች ወይን እንዲተክሉ፣ ዕርሻም እንዲያርሱ እዚያው ተዋቸው። 13ባቢሎናውያን የናስ ዐምዶቹን፣ በቤተ መቅደሱ ውስጥ የነበሩትን ተንቀሳቃሽ የዕቃ ማስቀመጫዎችንና ከናስ የተሠራውን የውሃ ማጠራቀሚያ ክብ በርሜል ሰባብረው ናሱን ወደ ባቢሎን ወሰዱ። 14እንዲሁም ምንቸቶቹን፣ መጫሪያዎቹን፣ መኰስተሪያዎቹን፣ ጭልፋዎቹን፣ በአጠቃላይም ከናስ የተሠሩትን የቤተ መቅደሱን መገልገያ ዕቃዎች ሁሉ ወሰዱ። 15የክብር ዘቡ አዛዥም ከንጹሕ ወርቅና ብር የተሠሩትን ጽናዎችና የመርጫ ወጭቶችን ወሰደ።

16ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገልገያ ብሎ ከናስ ያሠራቸው ሁለት ዐምዶች፣ የውሃ ማጠራቀሚያው ክብ በርሜልና ተንቀሳቃሽ የዕቃ ማስቀመጫዎቹ ክብደታቸው ከሚዛን በላይ ነበር። 17እያንዳንዱ ዐምድ ዐሥራ ስምንት ክንድ25፥17 8.1 ሜትር ያህል ነው። ሲሆን፣ የናስ ጕልላት ነበረው፤ የጕልላቱ ርዝመት ሦስት ክንድ25፥17 1.3 ሜትር ያህል ነው። ሆኖ፣ ዙሪያውን በሙሉ የናስ መርበብና የሮማን ፍሬዎች ቅርጽ ነበረው፤ ሌላውም ዐምድ ከነቅርጾቹ ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ ነበር።

18የክብር ዘብ አዛዡም ሊቀ ካህኑን ሠራያን፣ በማዕረግ ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ካህኑን ሶፎንያስንና ሦስቱን የበር ጠባቂዎች እስረኛ አድርጎ ወሰዳቸው። 19እስከዚያች ጊዜ ድረስ በከተማዪቱ ውስጥ ከቀሩትም የተዋጊዎቹን አለቃና አምስት የንጉሡን አማካሪዎች ወሰዳቸው። ደግሞም የአገሩን ሕዝብ ለውትድርና የሚመለምለውን ዋና የጦር አለቃ የነበረውን ጸሓፊውንና በከተማዪቱ ውስጥ የተገኙትን የጸሓፊውን ስድሳ ሰዎች ወሰዳቸው። 20አዛዡ ናቡዘረዳንም እነዚህን ሁሉ ይዞ ልብና ወዳለው ወደ ባቢሎን ንጉሥ አመጣቸው። 21ንጉሡም ሰዎቹን በሐማት ምድር እዚያው ልብና ውስጥ አስገደላቸው። ይሁዳም ከምድሩ በዚህ ሁኔታ ተማርኮ ሄደ።

22የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣ የሳፋን የልጅ ልጅ የሆነውን የአኪቃምን ልጅ ጎዶልያስን እዚያው በቀረው በይሁዳ ሕዝብ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው። 23መላው የሰራዊቱ ጦር አለቆችና ሰዎቻቸው የባቢሎን ንጉሥ፣ አገረ ገዥ አድርጎ ጎዶልያስን መሾሙን ሲሰሙ፣ እርሱ ወዳለበት ወደ ምጽጳ መጡ፤ እነርሱም የናታንያ ልጅ እስማኤል፣ የቃሬያም ልጅ ዮሐናን፣ የነጦፋዊው የተን ሑሜት ልጅ ሠራያ የማዕካታዊው ልጅ ያእዛንያና ሰዎቻቸው ነበሩ። 24ጎዶልያስም፣ “የባቢሎናውያንን ሹማምት አትፍሩ፤ እዚሁ አገር ኑሩ፤ የባቢሎንን ንጉሥ አገልግሉ፤ ሁሉም ነገር ይሳካላችኋል” ሲል ይህንኑ በቃለ መሐላ አረጋገጠላቸው። 25ነገር ግን በሰባተኛው ወር ንጉሣዊ ዝርያ የነበረው የኤሊሳማ የልጅ ልጅ የሆነው የናታንያ ልጅ እስማኤል ዐሥር ሰዎች ይዞ መጥቶ ጎዶልያስንና በምጽጳ አብረውት የነበሩትን የይሁዳን ሰዎችና ባቢሎናውያንን ገደለ። 26ባቢሎናውያንን ከመፍራታቸው የተነሣም ትንሽ ትልቅ ሳይባል ሕዝቡ ሁሉ ከሰራዊቱ የጦር አለቆች ጋር ወደ ግብፅ ሸሹ።

ዮአኪን ከእስራት ተፈታ

25፥27-30 ተጓ ምብ – ኤር 52፥31-34

27የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን በተማረከ በሠላሳ ሰባተኛው ዓመት፣ በዐሥራ ሁለተኛው ወር ከወሩም በሃያ ሰባተኛው ቀን ዮርማሮዴቅ25፥27 አሜል ማርዶክ ይባላል። በባቢሎን በነገሠ በዓመቱ ዮአኪንን ከእስራቱ ፈታው። 28በርኅራኄም መንፈስ አነጋገረው፤ በባቢሎን አብረውት ከነበሩት ነገሥታት ይልቅ ከፍ ያለውን የክብር ቦታ ሰጠው። 29ዮአኪንም የእስር ቤት ልብሱን ጣለ፤ እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ ከንጉሡ ማዕድ ዘወትር ይመገብ ጀመር፤ 30ንጉሡም ለዮአኪን እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ የዕለት ቀለቡን ይሰጠው ነበር።