但以理书 10 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

但以理书 10:1-21

底格里斯河边的异象

1波斯塞鲁士执政第三年,但以理,又名伯提沙撒,得到启示。这启示是真实的,是关于一场大争战的事。但以理通过异象明白了启示的意思。

2那时,我但以理悲伤了三个星期, 3期间没有吃过美味,没有尝过酒肉,没有抹过膏油。 4一月二十四日,我站在底格里斯河边, 5举目观看,见有一个人身穿细麻衣,腰束纯金的带子, 6身体如碧玉,面貌如闪电,眼睛如火炬,四肢如明亮的铜,声音如众人的呼喊。 7只有我但以理看见了这异象,跟我在一起的人都没有看见,但他们极其恐惧,纷纷逃匿, 8只剩下我一人观看这奇异的景象。我浑身无力,脸色苍白,精疲力尽。 9接着,我听见他说话的声音,一听见他的声音,我便俯伏在地上昏睡过去。 10忽然有一只手轻拍我,扶我用膝和手掌支撑起身体。 11他对我说:“倍受眷爱的但以理啊,要留心听我说,站起来吧,因为我是奉命到你这里来的。”他说完这话,我便战战兢兢地站起来。 12他说:“但以理啊,不要怕,从你在上帝面前谦卑地恳求明白这异象的第一天,你的祷告已蒙垂听。我是来答复你的。 13波斯国的守护神拦阻我二十一日。由于我滞留在波斯诸王那里,天使长米迦勒便来帮助我。 14我来是要使你明白将来你同胞的遭遇,因为这异象是关于将来的事。” 15他对我说话时,我低着头,说不出话。 16后来,有一位样子像人的用手摸我的嘴唇,我便开口对站在我面前的说:“我主啊,因为这异象,我痛苦不堪,毫无气力。 17仆人我怎能跟我主说话?我现在浑身无力,没有气息。”

18于是,那位样子像人的再次摸我,使我有力量。 19他对我说:“倍受眷爱的人啊,不要怕,愿你平安!要刚强勇敢。”我听到他的话,便有了力量,于是对他说:“我主啊,请说,因为你使我有了力量。” 20他说:“你知道我为什么要到你这里来吗?现在我要回去与波斯的守护神争战。我离开后,希腊的守护神就会来。 21除了你们的守护天使米迦勒以外,谁也不能帮助我抵挡他们。我来是要把记录在真理书上的事告诉你。

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 10:1-21

ዳንኤል በራእይ ያየው ሰው

1የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት፣ ብልጣሶር ለተባለው ዳንኤል ራእይ ታየው። መልእክቱ እውነት ነው፤ ስለ ታላቅ ጦርነትም የሚገልጽ ነበረ10፥1 ወይም እውነትና ከባድ ሸክም ነበር። መልእክቱንም ይገነዘብ ዘንድ በራእይ ማስተዋል ተሰጠው።

2በዚያን ጊዜ እኔ ዳንኤል ለሦስት ሳምንት አለቀስሁ፤ 3ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ምርጥ ምግብ አልበላሁም፤ ሥጋም ሆነ የወይን ጠጅ ወደ አፌ አልገባም፤ ቅባትም አልተቀባሁም።

4በመጀመሪያው ወር በሃያ አራተኛው ቀን፣ በታላቁ በጤግሮስ ወንዝ ዳር ቆሜ፣ 5ቀና ብዬ ስመለከት፣ በፊቴ በፍታ የለበሰና በወገቡም ላይ ምርጥ የወርቅ ቀበቶ የታጠቀ አንድ ሰው አየሁ። 6አካሉ እንደ ዕንቍ፣ ፊቱ እንደ መብረቅ፣ ዐይኖቹ እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹ እንደ ጋለ ናስ የሚያብረቀርቁ፣ ድምፁም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበር።

7ራእዩን ያየሁት እኔ ዳንኤል ብቻ ነበርሁ፤ ከእኔ ጋር የነበሩት ሰዎች አላዩም፤ ነገር ግን ታላቅ ፍርሀት ስለ ወደቀባቸው ሸሽተው ተደበቁ። 8ስለዚህ ይህን ታላቅ ራእይ እያየሁ ብቻዬን ቀረሁ፤ ምንም ጕልበት አልነበረኝም፤ መልኬ እጅጉን ገረጣ፤ ኀይልም አጣሁ። 9ከዚያም የቃሉን ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉንም ድምፅ በሰማሁ ጊዜ፣ በግንባሬ በምድር ላይ ተደፍቼ በከባድ እንቅልፍ ተዋጥሁ።

10እነሆም፣ አንድ እጅ ዳሰሰኝ፤ እየተንቀጠቀጥሁም በእጄና በጕልበቴ አቆመኝ፤ 11እርሱም፣ “እጅግ የተወደድህ ዳንኤል ሆይ፤ አሁን ወዳንተ ተልኬአለሁና፣ የምነግርህን አስተውል፤ ቀጥ ብለህም ቁም” አለኝ። ይህን ሲለኝም፣ እየተንቀጠቀጥሁ ተነሥቼ ቆምሁ።

12ደግሞም እንዲህ አለኝ፤ “ዳንኤል ሆይ፤ አትፍራ፣ ማስተዋልን ለማግኘትና በአምላክህም ፊት ራስህን ለማዋረድ ከወሰንህበት ከመጀመሪያው ቀን አንሥቶ ቃልህ ተሰምቷል፤ እኔም የቃልህን መልስ ይዤ መጥቻለሁ። 13ነገር ግን የፋርስ መንግሥት አለቃ ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ የሆነው ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም በዚያ ከፋርስ ንጉሥ ጋር ተውሁት። 14ራእዩ ሊፈጸም ገና ብዙ ዘመን ስለሚቀረው፣ ወደ ፊት በሕዝብህ ላይ የሚሆነውን ልገልጽልህ አሁን ወደ አንተ መጥቻለሁ።”

15ይህን እየተናገረኝ ሳለ፣ ፊቴን ወደ ምድር አቀረቀርሁ፤ የምናገረውንም ዐጣሁ። 16ከዚያም የሰው ልጅ የሚመስል10፥16 አብዛኛዎቹ ማሶሬቲክ የጥንት ቅጆች እንዲሁ ሲሆኑ፣ ከማሶሬቴክ አንድ የጥንት ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎችና ሰብዓ ሊቃናት ግን ከዚያም የሰው እጅ የሚመስል ነገር ይላሉ። ከንፈሮቼን ዳሰሰ፤ እኔም አፌን ከፈትሁ፤ መናገርም ጀመርሁ፤ በፊቴ የነበረውንም እንዲህ አልሁት፤ “ጌታዬ ሆይ፤ ከራእዩ የተነሣ ተሠቃይቻለሁ፤ ኀይልም ዐጣሁ። 17ጌታዬ ሆይ፤ ጕልበቴ ከዳኝ፤ መተንፈስም አቅቶኛል፤ እኔ አገልጋይህ ከአንተ ጋር መነጋገር እንዴት እችላለሁ?”

18እንደ ገናም፣ ሰው የሚመስለው ዳሰሰኝ፤ አበረታኝም። 19እርሱም፣ “እጅግ የተወደድህ ሰው ሆይ፤ አትፍራ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን፤ በርታ፤ ጽና” አለኝ።

እየተናገረኝም ሳለ፣ በረታሁና፣ “ጌታዬ ሆይ፤ አበርትተኸኛልና ተናገር” አልሁት።

20እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “ለምን ወደ አንተ እንደ መጣሁ ታውቃለህ? የፋርስን አለቃ ለመውጋት በቶሎ እመለሳለሁ፤ እኔም ስሄድ የግሪክ አለቃ ይመጣል። 21አስቀድሜ ግን በእውነት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ ከእነዚህ አለቆች ጋር ለመዋጋት ከአለቃችሁ ከሚካኤል በስተቀር የሚረዳኝ የለም።”