以赛亚书 61 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 61:1-11

大喜的讯息

1主耶和华的灵在我身上,因为耶和华膏立了我,

让我传福音给贫穷的人,

差遣我医治伤心的人,

宣告被掳的人得释放、

被囚的人得自由;

2宣告我们上帝耶和华的恩年和祂报仇的日子,

安慰一切悲哀的人;

3以华冠取代锡安哀伤者头上的灰尘,

以喜乐的膏油取代他们的哀伤,

以颂赞的外袍取代他们的沮丧。

他们将被称为耶和华所栽种的公义橡树,

以彰显祂的荣耀。

4他们必重修古老的荒场,

在久已毁坏之地重建荒废的城邑。

5异乡人要为你们牧放羊群,

外族人要为你们耕种田地、

照料葡萄园。

6你们要被称为耶和华的祭司,

我们上帝的臣仆。

你们必享用各国的财宝,

夸耀自己拥有他们的财富。

7你们曾经蒙受耻辱,

如今将得到双倍的福分;

你们曾经遭受屈辱,

如今将因得到产业而快乐。

你们将在自己的土地上得到双倍的福分,

享受永远的快乐。

8“因为我耶和华喜爱公正,

憎恶抢劫之罪。

我必凭信实赏赐我的子民,

与他们立永远的约。

9他们的后代必享誉列国,

子孙必名闻万邦,

看见的人都承认他们是蒙上帝赐福之民。”

10我因耶和华而无比喜乐,

因我的上帝而心里快乐,

因为祂给我穿上救恩的衣服、

披上公义的袍子,

使我像戴上华冠的新郎,

又像戴上饰物的新娘。

11大地怎样使嫩苗长出,

园子怎样使种子发芽,

主耶和华必照样使公义与颂赞在万民中滋长。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 61:1-11

የተወደደው የእግዚአብሔር ዓመት

1የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፤

ለድኾች የምሥራች እንድሰብክ፣

እግዚአብሔር ቀብቶኛል።

ልባቸው የተሰበረውን እንድጠግን፣

ለምርኮኞች ነጻነትን፣

ለእስረኞች መፈታትን እንዳውጅ61፥1 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ ዕውራንን ከጨለማ አወጣቸው ዘንድ ይላል። ልኮኛል፤

2የተወደደውን የእግዚአብሔርን ዓመት፣

የአምላካችንንም የበቀል ቀን እንዳውጅ፣

የሚያለቅሱትን ሁሉ እንዳጽናና ልኮኛል፤

3በጽዮን ያዘኑትን እንዳረጋጋ፣

በዐመድ ፈንታ፣

የውበት አክሊል እንድደፋላቸው፣

በልቅሶ ፈንታ፣

የደስታ ዘይት በራሳቸው ላይ እንዳፈስስላቸው፣

በትካዜ መንፈስ ፈንታ፣

የምስጋና መጐናጸፊያ እንድደርብላቸው ልኮኛል፤

እነርሱም የክብሩ መግለጫ እንዲሆኑ፣

እግዚአብሔር የተከላቸው፣

የጽድቅ ዛፎች ተብለው ይጠራሉ።

4የጥንት ፍርስራሾችን መልሰው ይሠራሉ፤

በቀድሞ ጊዜ የወደሙትን መልሰው ያቆማሉ፤

ከብዙ ትውልድ በፊት የወደሙትን

ፍርስራሽ ከተሞች እንደ ገና ይሠራሉ።

5መጻተኞች የበግ መንጎቻችሁን ያግዳሉ፤

ባዕዳን በዕርሻችሁና በወይን ተክል ቦታችሁ ላይ ይሠሩላችኋል።

6እናንተም የእግዚአብሔር ካህናት ተብላችሁ ትጠራላችሁ፤

የአምላካችን ባሮች ትባላላችሁ፤

የመንግሥታትን ሀብት ትመገባላችሁ፤

በብልጽግናቸውም ትኰራላችሁ።

7ሕዝቤ በኀፍረታቸው ፈንታ፣

ዕጥፍ ይቀበላሉ፤

በውርደታቸው ፈንታ፣

በርስታቸው ደስ ይላቸዋል፤

የምድራቸውንም ዕጥፍ ርስት ይወርሳሉ፤

ዘላለማዊ ደስታም የእነርሱ ይሆናል።

8“እኔ እግዚአብሔር ፍትሕን ስለምወድድ፣

ዝርፊያንና በደልን እጠላለሁ፤

በታማኝነቴም የሚገባቸውን እሰጣቸዋለሁ፤

ከእነርሱም ጋር የዘላለም ኪዳን አደርጋለሁ።

9ዘሮቻቸው በመንግሥታት፣

ልጆቻቸውም በሕዝቦች ዘንድ የታወቁ ይሆናሉ፤

የሚያዩአቸውም ሁሉ፣

እግዚአብሔር የባረካቸው ሕዝብ እንደ ሆኑ ያውቃሉ።”

10በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፤

ነፍሴ በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች፤

ሙሽራ ራሱን እንደሚያሳምር፣

ሙሽራዪቱም በዕንቈቿ እንደምታጌጥ፣

የድነትን ልብስ አልብሶኛል፤

የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛል።

11ምድር ቡቃያ እንደምታበቅል፣

የተክል ቦታ ችግኝ እንደሚያፈላ፣

ጌታ እግዚአብሔርም በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣

ጽድቅንና ምስጋናን ያበቅላል።