以赛亚书 5 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 5:1-30

葡萄园之歌

1我要为我所爱的歌唱,唱一首有关他葡萄园的歌:

我所爱的在肥美的山冈上有一个葡萄园。

2他松土,清除石头,

栽种了上好的葡萄,

在园中建了一座瞭望塔,

凿了榨酒池。

他期望收获好葡萄,

得到的却是坏葡萄。

3他说,“耶路撒冷犹大的居民啊,

请你们在我和葡萄园之间评评理。

4我不遗余力地料理葡萄园,

希望得到好葡萄,

为什么得到的只是坏葡萄呢?

5“现在,我告诉你们我会怎样处理这葡萄园,

我要除去篱笆,任它被毁坏;

我要拆毁围墙,任它被践踏。

6我不再修剪,不再锄地,

也不再降雨,

任由它荒废,长满荆棘和蒺藜。”

7万军之耶和华的葡萄园就是以色列

祂所喜爱的葡萄树就是犹大人。

祂希望看到公平,

却只看见杀戮;

指望看到公义,

却只听见冤声。

以色列的罪恶

8那些不断建房置田、占光土地、

独居其中的人有祸了!

9我亲耳听到万军之耶和华说:

“许多富丽堂皇的房屋必荒废,无人居住。

10三十亩葡萄园只产二十升酒,

二百公斤种子只产二十公斤粮食。”

11那些从清早到深夜贪杯好酒,

喝到酩酊大醉的人有祸了!

12席上,他们在琴、瑟、鼓、笛声中饮酒作乐,

却毫不理会耶和华的作为。

13所以,我的子民必因无知而被掳。

他们的贵族无饼充饥,

民众无水解渴。

14阴间必食欲膨胀,

张开大口吞噬耶路撒冷的首领、群众和宴乐之人。

15世人遭贬,降为卑下,

狂妄者眼目低垂。

16唯有万军之耶和华因祂的公正而受尊崇,

圣洁的上帝借公义彰显自己的圣洁。

17那时,羊群在那里吃草,

如在自己的草场,

寄居者在富人的荒场上进食。

18那些用虚假作绳子扯来罪恶,

用套绳拉来邪恶的人有祸了!

19他们说:“让上帝快点完成祂的工作,

好让我们看看;

以色列的圣者早点实现祂的计划,

好让我们知道。”

20那些善恶不分、黑白颠倒、

甜苦不辨的人有祸了!

21那些自以为聪明、睿智的人有祸了!

22那些以豪饮称霸、善于调酒的人有祸了!

23他们贪赃枉法,坑害无辜。

24他们的根必朽烂,

花朵如飞尘飘落,

就像火焰吞灭禾秸,烧尽干草,

因为他们厌弃以色列之圣者的训诲,

藐视万军之耶和华的言语。

25耶和华向祂的子民发怒,

伸手击打他们。

山岭震动,

他们横尸街头,犹如粪土。

然而,祂的怒气还没有止息,

祂降罚的手没有收回。

26祂必竖起旗帜召集远方的国家,

吹哨叫来地极的人。

看啊,他们必飞速而来!

27他们无人疲倦,无人踉跄,

无人打盹,无人睡觉,

都腰带紧束,鞋带未断。

28他们的利箭上弦,引弓待发;

他们的马蹄坚如岩石,

车轮快如旋风。

29他们吼叫如狮子,

像猛狮般咆哮着捕食,

将猎物叼走,无人能救。

30那日,他们必向以色列咆哮,

如怒海澎湃。

人若观看大地,

只见黑暗和艰难,

光明被密云遮盖。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 5:1-30

ስለ ወይን ቦታ የተነገረ ቅኔ

1ስለ ወዳጄ፣

ደግሞም ስለ ወይን ቦታው ልዘምር፤

ወዳጄ በለምለም ኰረብታ ላይ

የወይን ቦታ ነበረው።

2መሬቱን ቈፈረ፤ ድንጋይንም ለቅሞ አወጣ፤

ምርጥ የሆነውንም ወይን ተከለበት።

በመካከሉ መጠበቂያ ማማ ሠራ፤

የወይን መጭመቂያ ጕድጓድም አበጀ፤

ከዚያ መልካም ፍሬ ያፈራል ብሎ ዐሰበ፤

ነገር ግን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ።

3“እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤

በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ።

4ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምን

ሊደረግለት ይገባ ነበር?

መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬ

ስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ?

5እንግዲህ በወይኔ ቦታ

ምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤

ዐጥሩን እነቅላለሁ፤

ለጥፋት ይጋለጣል፤

ግንቡንም አፈርሳለሁ፣

መረጋገጫም ይሆናል።

6የማይኰተኰትና የማይታረም

ጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤

ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤

ዝናብም እንዳይዘንብበት

ደመናዎችን አዝዛለሁ።”

7የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር

የወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤

የይሁዳ ሰዎችም

የደስታው አትክልት ናቸው።

ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤

ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

ወዮታና ፍርድ

8ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣

ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣

መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣

ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣

የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።

10ከሩብ ጋሻ5፥10 በዕብራይስጥ፣ ሩብ ጋሻ መሬት በዐሥር ጥማድ በሬ በአንድ ቀን የሚታረስ ነው። የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል።”5፥10 ምናልባት አንድ ባዶስ ሀያ ሁለት ሊትር ያህል ነው። አንድ የቆሮስ መስፈሪያ መቶ ስድሳ ኪሎ ግራም ያህል ነው። አንድ የኢፍ መስፈሪያ ዐሥራ ስምንት ኪሎ ግራም ያህል ነው።

11የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋ

ማልደው ለሚነሡ፣

እስኪያነድዳቸውም ወይን በመጠጣት

ሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸው!

12በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣

ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤

ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤

ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም።

13ስለዚህ ሕዝቤ

ዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤

መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤

ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል።

14ስለዚህ ሲኦል5፥14 በዕብራይስጡ፣ መቃብር ማለት ነው። ሆዷን አሰፋች፣

አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤

መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋር

ወደዚያ ይወርዳሉ።

15ሰው ይዋረዳል፤

የሰው ልጅም ዝቅ ዝቅ ይላል፤

የእብሪተኛውም ዐይን ይሰበራል።

16የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን በፍትሕ ከፍ ከፍ ይላል፤

ቅዱሱም አምላክ ቅድስናውን በጽድቅ ይገልጻል።

17በጎችም በገዛ መሰማሪያቸው እንደሚሰማሩ ሆነው ይግጣሉ፤

የበግ ጠቦቶችም በባለጠጎች ፍርስራሽ ላይ ሣር ይበላሉ5፥17 በዕብራይስጡ፣ እንግዶች ይበሉታል ይለዋል።

18ኀጢአትን በማታለል ገመድ ለሚስቡ፣

በደልንም በሠረገላ ማሰሪያ ለሚጐትቱ ወዮላቸው!

19“በዐይናችን እንድናይ

እግዚአብሔር ይቸኵል፤

ሥራውንም ያፋጥን፤

የእስራኤልን ቅዱስ፣ የእርሱን ዕቅድ

እንድናውቃት ትቅረብ፤

ትምጣም” ለሚሉ ወዮላቸው!

20ክፉውን መልካም፣

መልካሙን ክፉ ለሚሉ

ብርሃኑን ጨለማ፣

ጨለማውን ብርሃን ለሚያደርጉ፣

ጣፋጩን መራራ፣

መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው!

21ራሳቸውን እንደ ብልኅ ለሚቈጥሩ፣

በራሳቸውም አመለካከት ጥበበኛ ለሆኑ ወዮላቸው!

22የወይን ጠጅ ለመጠጣት ጀግኖች፣

የሚያሰክር መጠጥ ለመደባለቅ ብርቱ ለሆኑ ወዮላቸው!

23ጕቦን በመቀበል በደለኛን ንጹሕ ለሚያደርጉ፣

ለበደል አልባ ሰው ፍትሕን ለሚነፍጉ ወዮላቸው!

24ስለዚህ የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣

ድርቆሽም በእሳት ጋይቶ እንደሚጠፋ፣

የእነርሱም ሥር እንዲሁ ይበሰብሳል፤

አበባቸውም እንደ ትቢያ ይበንናል፤

የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋልና፤

የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል አቃልለዋል።

25የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነድዷል፤

እጁን አንሥቶ መትቷቸዋል፤

ተራሮች ራዱ፤

ሬሳዎችም በመንገድ ላይ እንደ ተጣለ ጥራጊ ሆኑ፤

ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቍጣው ገና አልተመለሰም፤

እጁም እንደ ተነሣ ነው።

26ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትን

ምልክት ያቆማል፤

ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤

እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ።

27በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤

የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤

የወገባቸው መቀነት አይላላም፤

የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም።

28ፍላጻቸው የተሳለ፣

ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤

የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደ

ዐውሎ ነፋስ ናቸው።

29ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤

እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤

ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤

ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም።

30በዚያን ቀን

እንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤

ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣

ጨለማንና መከራን ያያል፤

ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።