以赛亚书 42 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 42:1-25

主的仆人

1“看啊,我所扶持、所拣选、所喜悦的仆人,

我已将我的灵赐给祂,

祂必将正义带给万邦。

2祂不喧嚷,不呼喊,

不在街上高声说话。

3压伤的芦苇,祂不折断;

将残的灯火,祂不吹灭。

祂必信实地带来正义。

4祂不灰心也不沮丧,

直到祂在地上设立正义。

四海都渴望祂的训诲。”

5创造诸天、铺展穹苍、

设立大地和地上的一切、

赐给世人生命气息和灵性的耶和华上帝说:

6“我耶和华凭公义呼召你,

我必扶持你,保护你,

使你做我与众民立约的中保、

成为列国的光,

7使你开瞎子的眼睛、

从监牢中释放囚犯、

领出陷在黑暗中的人。

8我是耶和华,这就是我的名字。

我不会把我的荣耀给假神,

也不会把我当受的赞美给雕刻的偶像。

9看啊,以前的预言都已应验,

我现在要宣告新的预言,

把还未发生的事告诉你们。”

赞美主的歌

10航海的和海中的一切、

众海岛和岛上的居民啊,

你们要向耶和华高唱新歌,

从地极赞美祂。

11旷野和其中的城邑以及基达人居住的村庄,

要一同扬声颂赞。

西拉的居民要歌唱,

在山顶欢呼。

12愿他们把荣耀归给耶和华,

在众海岛上颂赞祂。

13耶和华像出征的勇士,

像斗志激昂的战士。

祂必高呼吶喊,战胜仇敌。

上帝应许帮助以色列人

14“我已沉默多时,我克制不语,

现在我要发出急促的呐喊,

像分娩的妇人。

15我要使大山小丘一片荒凉,

上面的草木都枯萎。

我要使河川变成岛屿,

池塘干涸。

16我要带领瞎子走他们不认识的路,

引导他们走陌生的道。

我要把他们面前的黑暗变为光明,

坎坷之地变得平坦。

我必行这些事,我必不离弃他们。

17但那些信靠雕刻的偶像、

供奉金属铸像的必遭唾弃,

羞愧难当。

以色列眼瞎耳聋

18“耳聋的人啊,听吧!

眼瞎的人啊,看吧!

19有谁比我的仆人更瞎,

比我差遣的使者更聋呢?

有谁像那些与我立约的人那样瞎呢?

有谁像耶和华的仆人那样瞎呢?

20你们看见许多事却不领会,

耳朵开着却听不见。”

21耶和华乐意使祂的律法尊大而荣耀,

因为祂行事公义。

22但这些百姓饱受劫掠,

都被困在坑中,囚在监内。

他们沦为俘虏,无人搭救;

被当作战利品掳走,无人追回。

23你们当中谁肯专心听呢?

以后谁肯留心倾听呢?

24谁把雅各交给了掳掠者,

使以色列任人劫掠?

难道不是被我们得罪的耶和华吗?

他们不肯遵行祂的道,

也不听从祂的训诲。

25所以,祂把烈怒和战火倾倒在他们身上。

他们被火包围,却不明白;

被烈火焚身,却不在乎。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 42:1-25

የእግዚአብሔር አገልጋይ

1“ደግፌ የያዝሁት አገልጋዬ፣

በእርሱም ደስ የሚለኝ ምርጤ ይህ ነው፤

መንፈሴን በእርሱ ላይ አደርጋለሁ፤

ለአሕዛብም ፍትሕን ያመጣል።

2አይጮኽም፣ ቃሉን ከፍ አያደርግም፤

ድምፁን በመንገድ ላይ በኀይል አያሰማም።

3የተቀጠቀጠ ሸምበቆ አይሰብርም፤

የሚጤስም የጧፍ ክር አያጠፋም፤

ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።

4ፍትሕን በምድር እስኪያመጣ ድረስ፣

አይደክምም፤ ተስፋም አይቈርጥም፤

ደሴቶች በሕጉ ይታመናሉ።”

5ሰማያትን የፈጠረ፣ የዘረጋቸውም፣

ምድርንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ ያበጀ፣

ለሕዝቧ እስትንፋስን፣

ለሚኖሩባትም ሕይወትን የሚሰጥ፣

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

6“እኔ እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፤

እጅህንም እይዛለሁ፤

እጠብቅሃለሁ፤

ለሕዝቡ ቃል ኪዳን፣

ለአሕዛብም ብርሃን አደርግሃለሁ።

7የዕውሮችን ዐይን ትከፍታለህ፤

ምርኮኞችን ከእስር ቤት፣

በጨለማ የተቀመጡትንም ከወህኒ ታወጣለህ።

8“እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜም ይህ ነው፤

ክብሬን ለሌላ፣

ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም።

9እነሆ፤ የቀድሞው ነገር ተፈጽሟል፤

እኔም አዲስ ነገር እናገራለሁ፤

ከመብቀሉም በፊት፣

ለእናንተ አስታውቃለሁ።”

ለእግዚአብሔር የውዳሴ መዝሙር

10እናንት ወደ ባሕር የምትወርዱ፣ በዚያም ያላችሁ ሁሉ፣

ደሴቶችና በዚያ የምትኖሩ በሙሉ፣

ለእግዚአብሔር አዲስ መዝሙር፣

ከምድር ዳርቻም ምስጋናውን ዘምሩ።

11ምድረ በዳውና ከተሞቹ ድምፃቸውን ከፍ ያድርጉ፤

ቄዳር ያለችበት መንደር ደስ ይበለው፤

የሴላ ሕዝቦች በደስታ ይዘምሩ፤

ከተራሮችም ራስ ላይ ይጩኹ።

12ክብር ለእግዚአብሔር ይስጡ፤

ምስጋናውንም በደሴቶች ያውጁ።

13እግዚአብሔር እንደ ኀያል ሰው ይዘምታል፤

እንደ ተዋጊ በወኔ ይነሣል፤

የቀረርቶ ጩኸት ያሰማል፤

ጠላቶቹንም ድል ያደርጋል።

14“ለረዥም ጊዜ ዝም አልሁ፤

ጸጥ አልሁ፤ ራሴንም ገታሁ፤

አሁን ግን ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

እጮኻለሁ፤ ቍና ቍና እቃትታለሁ፤ እተነፍሳለሁ።

15ተራራውንና ኰረብታውን አፈርሳለሁ፤

ዕፀዋቱን ሁሉ አደርቃለሁ፤

ወንዙንም ደሴት አደርጋለሁ፤

ኵሬውን አደርቃለሁ።

16ዕውሮችን በማያወቁት መንገድ

እመራቸዋለሁ፤

ባልተለመደ ጐዳና እወስዳቸዋለሁ።

ጨለማውን በፊታቸው ብርሃን አደርጋለሁ፤

ጐርባጣውን ስፍራ አስተካክላለሁ።

ይህን አደርጋለሁ፤

አልተዋቸውም።

17በጣዖት የሚታመኑ ግን፣

ምስሎችን፣ ‘አምላኮቻችን ናችሁ’ የሚሉ፣

ወደ ኋላቸው ይመለሳሉ፤ ፈጽመው ይዋረዳሉም።

ዕውሯና ደንቈሮዋ እስራኤል

18“እናንት ደንቈሮዎች ስሙ፤

እናንት ዕውሮች እዩ፤ ተመልከቱም።

19አገልጋዬ እንጂ፣ ሌላ ዕውር ማን አለ?

ከምልከው መልእክተኛዬስ በቀር ማን ደንቈሮ አለ?

ለእኔ ታማኝ እንደ ሆነ ሰው የታወረ፣

እንደ እግዚአብሔርስ አገልጋይ ዕውር ማነው?

20ብዙ ነገርን አያችሁ፤ ነገር ግን አላስተዋላችሁም፤

ጆሯችሁ ክፍት ነው፤ ነገር ግን ምንም አትሰሙም።”

21እግዚአብሔር ስለ ጽድቁ ሲል፣

ሕጉን ታላቅና የተከበረ በማድረግ ደስ

አለው።

22ይህ ሕዝብ ግን የተበዘበዘና የተዘረፈ፣

በጕድጓድ ውስጥ የተጠመደበት፣

በወህኒ ቤት የተዘጋበት ነው፤

ተበዝብዘዋል፣

የሚያድናቸውም የለም፤

ተማርከዋል፣

“መልሷቸው” የሚልም የለም።

23ከእናንተ ይህን የሚሰማ፣

ለሚመጣውም ጊዜ አስተውሎ የሚያደምጥ ማነው?

24ያዕቆብን ለዝርፊያ፣

እስራኤልን ለምርኮ የዳረገ ማነው?

በኀጢአት የበደልነው፣

እግዚአብሔር አይደለምን?

መንገዱን ለመከተል፣

ለሕጉም መታዘዝ አልፈለጉምና።

25ስለዚህ የሚነድድ ቍጣውን፣

የጦርነትንም መዓት አፈሰሰባቸው፤

በእሳት ነበልባል ከበባቸው፤ እነርሱ ግን አላስተዋሉም፤

አቃጠላቸው፤ እነርሱ ግን ልብ አላሉም።