以赛亚书 4 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 4:1-6

1那时,七个女人将拉着一个男人,说:“我们会负责自己的吃穿,只求你娶我们,让我们归在你名下,好除掉我们嫁不出去的羞辱。”

耶路撒冷的复兴

2到那日,耶和华的苗必长得茂盛华美,这地方的出产必成为以色列幸存者的骄傲和光荣。 3-4主必以公义的灵和焚烧的灵洗净锡安的污秽,清除耶路撒冷的血迹。所有锡安剩余的人,即留在耶路撒冷、名字记录在生命册上的人都将被称为圣洁之民。 5耶和华必在日间用烟云遮蔽整个锡安山和那里的会众,在夜间用火光照亮他们。祂的荣耀必遮盖一切, 6是白日避暑的亭子,是躲避狂风暴雨的避难所和藏身处。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 4:1-6

1በዚያን ቀን ሰባት ሴቶች

አንዱን ወንድ ይዘው፣

“የራሳችንን ምግብ እንበላለን፤

የራሳችንንም ልብስ እንለብሳለን፤

በአንተ ስም ብቻ እንጠራና፣

ውርደታችንን አስቀርልን” ይሉታል።

የእግዚአብሔር ዛፍ ቅርንጫፍ

2በዚያን ቀን የእግዚአብሔር ዛፍ ቅርንጫፍ ያማረና የከበረ ይሆናል፤ የምድሪቱም ፍሬ ከጥፋት ለተረፈው የእስራኤል ወገን ኵራትና ክብር ይሆናል። 3በጽዮን የቀሩት፣ በኢየሩሳሌምም የተረፉት፣ በኢየሩሳሌም በሕይወት ከተመዘገቡት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ተብለው ይጠራሉ። 4ጌታ የጽዮንን ሴቶች እድፍ ያጥባል፤ ኢየሩሳሌምንም ከተነከረችበት ደም በፍርድና በሚያቃጥል መንፈስ4፥4 ወይም በእግዚአብሔር መንፈስ ማለት ነው። ያነጻታል። 5ከዚያም እግዚአብሔር በጽዮን ተራራ ላይና በዚያ በሚሰበሰቡትም ሁሉ ላይ በቀን ደመናንና ጢስን፣ በሌሊትም የሚንበለበለውን የእሳት ብርሃን ይፈጥራል፤ በክብሩ ሁሉ ላይ መጋረጃ ይሆናል፤ 6ከቀኑ ሙቀት ጥላና መከለያ፣ ከውሽንፍርና ከዝናብም መጠጊያና መሸሸጊያ ስፍራ ይሆናል።