以赛亚书 33 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 33:1-24

主必拯救锡安

1你们这些毁灭别人、自己还未被毁灭的人有祸了!

等你们毁灭完了,就毁灭你们。

你们这些欺诈别人、自己还未被欺诈的人有祸了!

等你们欺诈完了,就欺诈你们。

2耶和华啊,求你施恩给我们,

我们等候你。

求你每天早晨都作我们的力量,

在艰难的时候拯救我们。

3你大喊一声,列邦都奔逃;

你一站起来,列国都溃散。

4他们的战利品必被拿走,

就像谷物被蝗虫吃掉一样;

人们像蝗虫一样扑向他们的战利品。

5耶和华受尊崇,

因为祂住在高天之上,

祂必使锡安充满公平和公义。

6祂必成为你一生的保障,

使你得到丰盛的救恩、智慧和知识。

敬畏耶和华是你最大的宝藏。

7看啊,他们的勇士在街上哀号,

求和的使者悲痛哭泣。

8大路荒凉,行人绝迹。

条约被废,城邑被弃,

人民遭藐视。

9地上一片荒凉,

黎巴嫩的树木枯干,

沙仑好像旷野,

巴珊迦密的树叶凋零。

10耶和华说:

“我现在要施展大能,

我必受尊崇。

11你们所谋的像糠秕,

所行的如碎秸,毫无价值。

你们的气息会像火一样烧灭你们自己。

12列邦必被烧成灰烬,

好像割下的荆棘被火焚烧。”

13远方的人啊,

要听一听我的作为。

近处的人啊,

要承认我的大能。

14锡安的罪人恐惧,

不敬虔的人颤抖。

他们说:“我们谁能住在烈火中呢?

谁能住在永不止息的火焰里呢?”

15秉公行义、说话正直、

憎恶不义之财、不受贿赂、

掩耳不听害人之谋、

闭眼不看邪恶之事的人,

16才可以住在高处。

他们的堡垒是坚固的磐石,

他们必不会绝粮断水。

17你们必目睹君王的荣美,

看到辽阔的土地,

18你们必想起以往可怕的情景,

说:“登记人口的在哪里?

收贡银的在哪里?

数城楼的在哪里?”

19你们再也看不见那些残暴之徒了,

他们的言语奇怪、陌生、

无法听懂。

20你们看锡安——我们守节期的城!

你们必看见耶路撒冷成为安宁之地,

像一个永不挪移的帐篷,

橛子永不拔出,

绳索也不会断。

21在那里,威严的耶和华必与我们同在。

那里必如巨川大河流经之地,

敌人的大小船只都无法穿过。

22因为耶和华是我们的审判官,

是我们的立法者,

是我们的君王,

是我们的拯救者。

23敌人的帆索松开,

桅杆晃动不稳,

风帆无法扬起。

那时,大量的战利品将被瓜分,

甚至瘸子都分得一份。

24耶路撒冷必没有居民说:

“我生病了”,

城中百姓的罪恶必得到赦免。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 33:1-24

የጭንቅ ጊዜና ርዳታ

1አንተ ሳትጠፋ የምታጠፋ፣

አንት አጥፊ፣ ወዮልህ!

አንተ ሳትካድ የምትክድ፣

አንት ከዳተኛ፣ ወዮልህ!

ማጥፋትን በተውህ ጊዜ፣

ትጠፋለህ፤

ክሕደትህንም በተውህ ጊዜ ትከዳለህ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረን፤

አንተን ተስፋ አድርገናል።

በየማለዳው ብርታት፣

በጭንቅ ጊዜም ድነት ሁነን።

3ሕዝቦች በድምፅህ ነጐድጓድ ይሸሻሉ፤

መንግሥታት ስትነሣ ይበተናሉ።

4ሕዝቦች ሆይ፤ አንበጣ እንደሚሰበስብ ብዝበዛችሁም ይሰበሰባል፤

ሰዎችም እንደ ኵብኵባ ይጨፍሩበታል።

5እግዚአብሔር በአርያም ተቀምጧልና ከፍ ከፍ አለ፤

ጽዮንን በጽድቅና በፍትሕ ይሞላታል።

6እርሱ ለዘመንህ የሚያስተማምን መሠረት፣

የድነት፣ የዕውቀትና የጥበብ መዝገብ ይሆናል፤

እግዚአብሔርንም መፍራት የዚህ ሀብት ቍልፍ ነው33፥6 ወይም እግዚአብሔርን መፍራት ከእግዚአብሔር የሆነ ሀብት ነው

7እነሆ፤ ጐበዞቻቸው በየመንገዱ ይጮኻሉ፤

የሰላም መልእክተኞችም አምርረው ያለቅሳሉ።

8አውራ ጐዳናዎች ባዶ ናቸው፤

በመንገድ ላይ ሰው የለም፤

ስምምነቱ ፈርሷል፤

መካሪዎቹ33፥8 የሙት ባሕር ጥቅልሎች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ከተሞች ይላል። ተንቀዋል፤

የሚከበርም የለም።

9ምድሪቱ አለቀሰች33፥9 ወይም ደረቀች (ጠወለገች)፤ መነመነች፤

ሊባኖስ ዐፈረች፤ ጠወለገች፤

ሳሮን እንደ ዓረባ ምድረ በዳ ሆነች፤

ባሳንና ቀርሜሎስ ቅጠላቸውን አረገፉ።

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “አሁን እነሣለሁ፤

አሁን ከፍ ከፍ እላለሁ፤

አሁን እከብራለሁ።

11ገለባን ፀነሳችሁ፤

እብቅንም ወለዳችሁ፤

እስትንፋሳችሁም የሚበላችሁ እሳት ነው።

12ሕዝቦች ኖራ እንደሚወጣው ድንጋይ ይቃጠላሉ፤

እንደ እሾኽ ቍጥቋጦ በእሳት ይጋያሉ።”

13እናንት በሩቅ ያላችሁ ያደረግሁትን ስሙ፤

እናንት በቅርብ ያላችሁ ኀይሌን ዕወቁ!

14በጽዮን ያሉ ኀጢአተኞች ደነገጡ፤

አምላክ የሌላቸውም ፍርሀት ይዟቸው፣

“ከእኛ መካከል ከሚባላ እሳት ጋር ማን መኖር ይችላል፣

ከዘላለም እሳትስ ጋር ማን መኖር ይችላል?” አሉ።

15በጽድቅ የሚራመድ፣

ቅን ነገር የሚናገር፣

በሽንገላ የሚገኝን ትርፍ የሚንቅ፣

መማለጃን ላለመቀበል እጁን የሚሰበስብ፣

የግድያን ሤራ ላለመስማት ጆሮውን የሚደፍን፣

ክፋትን ላለማየት ዐይኑን የሚጨፍን፣

16ይህ ሰው በከፍታ ላይ ይኖራል፤

የተራራም ምሽግ መጠጊያው ይሆናል፤

እንጀራ ይሰጠዋል፣

ውሃውም አይቋረጥበትም።

17ዐይኖችህ ንጉሡን በውበቱ ያዩታል፤

በሩቅ የተዘረጋችውንም ምድር ይመለከታሉ።

18የቀደመው መከራ ትዝ እያለህ፣

“ያ ዋና አለቃ የት አለ?

ግብር ተቀባዩስ ወዴት ሄደ?

የመጠበቂያ ማማ ኀላፊውስ የት አለ?” ትላለህ።

19እነዚያ ንግግራቸው የማይገባ፣

የሚሉትም የማይታወቅ፣

ሊረዱት የማይቻል ቋንቋ የሚናገሩትን ጋጠወጥ ሕዝብ ከእንግዲህ አታያቸውም።

20በዓላታችንን የምናከብርባትን ከተማ ጽዮንን ተመልከት፤

ሰላማዊ መኖሪያ፣ የማትነቃነቅ ድንኳን የሆነችውን፣

ካስማዋ የማይነቀል፣

ከገመዷ አንዱ እንኳ የማይበጠሰውን፣

ኢየሩሳሌምን ዐይኖችህ ያያሉ።

21እግዚአብሔር በዚያ ኀይላችን ይሆናል፤

ባለ መቅዘፊያ ጀልባዎች እንደማያልፉባቸው፣

ታላላቅ መርከቦችም እንደማይሻገሯቸው፣

ሰፋፊ ወንዞችና ጅረቶች ይሆንልናል።

22እግዚአብሔር ዳኛችን ነው፤

እግዚአብሔር ሕግ ሰጪያችን ነው፤

እግዚአብሔር ንጉሣችን ነው፤

የሚያድነንም እርሱ ነውና።

23መወጠሪያ ገመድህ ላልቷል፤

ምሰሶው ጠብቆ አልተተከለም፤

ሸራው አልተወጠረም፤

በዚያ ጊዜ ታላቅ ምርኮ ይከፋፈላል፤

ዐንካሳ እንኳ ሳይቀር ምርኮ ይወስዳል።

24በጽዮን ተቀምጦ፣ “ታምሜአለሁ” የሚል አይኖርም፤

በዚያ የሚኖሩ ሰዎች ኀጢአትም ይቅር ይባላል።