以赛亚书 29 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 29:1-24

耶路撒冷被围

1耶和华说:“亚利伊勒29:1 亚利伊勒”在此处用来指锡安/耶路撒冷,2节、7节同。亚利伊勒

大卫安营的城啊!

你有祸了!

尽管你年复一年地守节期,

2我还是要叫你受苦。

你必悲伤哀号,

在我面前成为一座祭坛。

3我必把你团团围住,

屯兵围困你,

修筑高台攻打你。

4你必一败涂地,

躺在尘土中说话,

你细微的声音从土中传来,

好像地下幽灵的声音。

你耳语般的低声从土中传来。

5但你的众仇敌必像纤细的尘埃一样消散,

众多的残暴之徒必如被风刮去的糠秕。

突然,刹那之间,

6万军之耶和华必带着雷轰、地震、巨响、旋风、暴风和烈火来临。

7攻打、围困耶路撒冷及其堡垒的各国军队必如梦幻,

如夜间的异象一样消失。

8他们好像饥饿的人梦中吃饭,

醒来仍然饥饿;

像口渴的人梦中喝水,

醒来仍然渴得发昏。

攻打锡安山的各国军队结局都必如此。”

9你们驻足惊奇吧!

你们自我蒙蔽,继续瞎眼吧!

你们醉了,但不是因为酒;

你们东倒西歪,但不是因为烈酒。

10因为耶和华把沉睡的灵倾倒在你们身上,

祂封住你们的眼睛,

盖住你们的头。

你们的眼睛就是先知,

你们的头就是先见。

11对你们而言,所有的启示都好像封了印的书卷。你们把书卷交给识字的人读,他会说:“我不能读,这书卷是封着的。” 12你们把书卷交给不识字的人读,他会说:“我不识字。”

13主说:“这些人嘴上亲近我,

尊崇我,心却远离我。

他们敬拜我不过是遵行人定的规条。

14所以,我要再次行奇妙无比的事,使他们震惊。

他们智者的智慧必泯灭,

明哲的聪明必消失。”

15那些向耶和华深藏计谋的人有祸了!

他们暗中行事,

自以为无人看见也无人知道。

16他们太愚蠢了!

窑匠怎能跟泥土相提并论?

被造的怎能对造它的说:

“你没有造我”?

陶器怎能对陶匠说:

“你什么也不懂”?

17再过不久,黎巴嫩将变成沃野,

沃野上庄稼茂密如林。

18那时,聋子必听见那书卷上的话,

黑暗中的瞎子必能看见。

19卑微的人必因耶和华而欢喜,

贫穷的人必因以色列的圣者而快乐。

20残暴之徒必消失,

嘲讽者必绝迹,

所有心怀不轨者必被铲除。

21他们诬陷人,

暗算审判官,

冤枉无辜。

22因此,关于雅各家,

救赎亚伯拉罕的耶和华说:

雅各的子孙必不再羞愧,

脸上再无惧色。

23因为他们看见我赐给他们的子孙时,

必尊我的名为圣,

必尊雅各的圣者为圣,

必敬畏以色列的上帝。

24心里迷惘的必明白真理,

发怨言的必欣然受教。”

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 29:1-24

ወዮ ለዳዊት ከተማ

1ዳዊት የሰፈረብሽ ከተማ፣

አርኤል፣ አርኤል ወዮልሽ!

ዓመት በዓመት ላይ ጨምሪ፣

ዐውደ ዓመትሽም ይቀጥል።

2ነገር ግን አርኤልን29፥2 በዕብራይስጡ፣ የመሠዊያ መሬት የሚለው ቃል ድምፀት፣ አርኤል ከሚለው ቃል ጋር አንድ ዐይነት ነው። እከብባለሁ፤

ታለቅሳለች፤ ዋይ ዋይ ትላለች፤

ለእኔም እንደ መሠዊያ ስፍራ ትሆንልኛለች።

3በዙሪያሽ እሰፍራለሁ፤

በቅጥር እከብብሻለሁ፤

የከበባ ዐምባም ሠርቼ አስጨንቅሻለሁ።

4ወደ ታች ትወርጃለሽ፤ ከምድርም በታች ትናገሪያለሽ፤

ንግግርሽ ከትቢያ እየተጕተመተመ ይወጣል፤

ድምፅሽ እንደ መናፍስት ድምፅ ከመሬት ወደ ላይ ይመጣል፤

ንግግርሽ ከትቢያ ያንሾካሹካል።

5ነገር ግን ብዙ ጠላቶችሽ እንደ ትቢያ ብናኝ፣

የጨካኞች መንጋ በነፋስ እንደሚነዳ

ገለባ ይሆናሉ።

ድንገት ሳይታሰብም፣

6የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በነጐድጓድ፣ በምድር መናወጥና በታላቅ ድምፅ፣

በዐውሎ ነፋስና በኀይለኛ ሞገድ፣ ፈጽሞ በሚባላም የእሳት ነበልባል ይመጣል።

7አርኤልን የሚወጋ የአሕዛብ ሁሉ መንጋ፣

በእርሷና በምሽጓ ላይ አደጋ የሚጥልና የሚከብባት፣

እንደ ሕልም

በሌሊትም እንደሚታይ ራእይ ይሆናል።

8የተራበ ሰው በሕልሙ ሲበላ ዐድሮ፣

ነገር ግን ሲነቃ ራቡ እንዳልለቀቀው፣

የጠማውም ሰው በሕልሙ ሲጠጣ ዐድሮ፣

ነገር ግን ሲነቃ እንደ ዛለና ጥማቱም እንዳልተወው፣

የጽዮንን ተራራ የሚወጋ፣

የአሕዛብ መንጋ ሁሉ እንዲሁ ይሆናል።

9ነኹልሉ ተደነቁም፤

ተጨፈኑ፤ እስከ ወዲያኛውም ታውራችሁ ቅሩ፤

በወይን ጠጅ አይሁን እንጂ ስከሩ፤

በሚያሰክር መጠጥ አይሁን እንጂ ተንገዳገዱ።

10እግዚአብሔር ከባድ እንቅልፍ ጥሎባችኋል፤

ዐይኖቻችሁን፣ ነቢያትን ጨፍኖባችኋል፤

ራሶቻችሁን፣ ባለ ራእዮችን ሸፍኖባችኋል።

11ይህ ሁሉ ራእይ በጥቅልል መጽሐፍ ውስጥ እንደ ታሸገ ቃል ሆኖባችኋል። ጥቅልሉንም መጽሐፍ ማንበብ ለሚችል ሰው፣ “እባክህ አንብብልን” ብላችሁ ብትሰጡት፣ “ታሽጓልና አልችልም” ይላችኋል። 12ደግሞም ጥቅልሉን መጽሐፍ ማንበብ ለማይችል ሰው፣ “እባክህን አንብብልን” ብላችሁ ብትሰጡ፣ “ማንበብ አልችልም” ይላችኋል።

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባል፤

በከንፈሩም ያከብረኛል፤

ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው፤

የሚያመልከኝም፣

ሰው ባስተማረው ሰው ሠራሽ ሥርዐት ብቻ ነው29፥13 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ በከንቱ ያመልኩኛል፤ ትምህርታቸው ሰው ያሰተማረው ሰው ሠራሽ ሥርዐት ብቻ ነው ይላል።

14ስለዚህ ይህን ሕዝብ በድንቅ ላይ ድንቅ

ነገር እያደረግሁ፣

ዳግመኛ አስገርመዋለሁ፤

የጥበበኞች ጥበብ ይጠፋል፤

የአስተዋዮችም ማስተዋል ይበንናል።”

15ሐሳባቸውን ከእግዚአብሔር ለመደበቅ፣

ወደ ጥልቅ ጕድጓድ ለሚወርዱ

ሥራቸውንም በጨለማ ለሚያከናውኑ፣

“ማን ያየናል? ማንስ ያውቅብናል” ለሚሉ ወዮላቸው!

16እናንተ ነገሮችን ትገለብጣላችሁ

ሸክላ ሠሪውን እንደ ሸክላ ትመለከታላችሁ፤

ለመሆኑ፣ ተሠሪ ሠሪውን፣

“እርሱ አልሠራኝም” ይለዋልን?

ሸክላ የሠራውን፣

“እርሱ ምንም አያውቅም” ይለዋልን?

17ሊባኖስ ወደ ለም ዕርሻነት ለመለወጥ፣

ለም የሆነውም መሬት ወደ ዱርነት ለመለወጥ ጥቂት ጊዜ አልቀረውምን?

18በዚያን ጊዜ ደንቈሮ የጥቅልሉን መጽሐፍ ቃል ይሰማል፤

የዐይነ ስውሩም ዐይኖች

ከጭጋግና ከጨለማ ተላቀው ያያሉ።

19ትሑታን በእግዚአብሔር

ምስኪኖችም በእስራኤል ቅዱስ እንደ ገና ሐሤት ያደርጋሉ።

20ጨካኞች እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤

ፌዘኞችም በንነው ይጠፋሉ፤

ለክፋት ያደፈጡ ሁሉ ይወገዳሉ።

21ሰውን በነገር በደለኛ የሚያደርጉ፣

በተከሳሽ ላይ ወጥመድ የሚዘረጉ፣

በሐሰት ምስክር ፍትሕን ከንጹሓን የሚቀሙ ይቈረጣሉ።

22ስለዚህ አብርሃምን የተቤዠው እግዚአብሔር

ለያዕቆብ ቤት እንዲህ ይላል፤

“ያዕቆብ ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም፤

ፊቱም ከእንግዲህ አይለዋወጥም።

23በመካከላቸው የእጄ ሥራ የሆኑ፣

ልጆቻቸውን ሲያዩ፣

ስሜን ይቀድሳሉ፤

የያዕቆብን ቅዱስ ቅድስና ያውቃሉ፤

በእስራኤልም አምላክ ፊት በፍርሀት ይቆማሉ።

24በመንፈስ የሳቱ ያስተውላሉ፤

የሚያጕረመርሙም ምክር ይቀበላሉ።”