以赛亚书 13 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 13:1-22

预言审判巴比伦

1以下是亚摩斯的儿子以赛亚得到有关巴比伦的预言:

2要在光秃的山顶上竖立旗帜,

向战士高呼,

挥手示意他们进攻贵族居住的城。

3我已向我拣选的士兵发出命令,

我已号召我的勇士去倾倒我的烈怒,

他们因我的胜利而欢喜。

4听啊,山上人声鼎沸,

像是大军的声音。

那是列邦列国聚集呐喊的声音。

万军之耶和华正在召集军队,

准备作战。

5他们从地极,从天边而来。

那是耶和华及倾倒祂烈怒的兵器,

要来毁灭大地。

6哀号吧!

耶和华的日子近了,

全能者施行毁灭的时候到了。

7人们都必双手发软,胆战心惊,

8惊恐万状,

痛苦不堪如同分娩的妇人。

他们必面面相觑,

羞愧得面如火烧。

9看啊,耶和华的日子来临了,

是充满愤恨和烈怒的残酷之日,

要使大地荒凉,

毁灭地上的罪人。

10天上的星辰不再发光,

太阳刚出来就变黑,

月亮也暗淡无光。

11我必惩罚这罪恶的世界,

惩治邪恶的世人,

制止骄横之人的狂妄,

压下残暴之徒的骄傲。

12我必使人比精炼的金子还稀少,

俄斐的纯金更罕见。

13我万军之耶和华发烈怒的日子,

必震动诸天,

摇撼大地。

14人们都投奔亲族,

逃回故乡,

好像被追赶的鹿,

又如走散的羊。

15被捉住的人都会被刺死,

被逮住的人都会丧身刀下。

16他们的婴孩将被摔死在他们眼前,

家园遭劫掠,

妻子被蹂躏。

17看啊,我要驱使玛代人来攻击他们。

玛代人不在乎金子,

也不看重银子,

18他们必用弓箭射死青年,

不怜悯婴儿,

也不顾惜孩童。

19巴比伦在列国中辉煌无比,

迦勒底人的荣耀,

但上帝必毁灭她,

好像毁灭所多玛蛾摩拉一样。

20那里必人烟绝迹,

世世代代无人居住,

没有阿拉伯人在那里支搭帐篷,

也无人牧放羊群。

21那里躺卧着旷野的走兽,

咆哮的猛兽占满房屋;

鸵鸟住在那里,

野山羊在那里跳跃嬉戏。

22豺狼在城楼上嚎叫,

野狗在宫殿里狂吠。

巴比伦的结局近了,

它的时候不多了!

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 13:1-22

በባቢሎን ላይ የተነገረ ትንቢት

1የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ባቢሎን ያየው ንግር፤

2በተራቈተ ኰረብታ ዐናት ላይ ምልክት ስቀሉ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጩኹ፤

በመሳፍንቱም በር እንዲገቡ፣

በእጅ ምልክት ስጡ።

3በድል አድራጊነቴ ደስ የሚላቸውን ቅዱሳኔን አዝዛለሁ፤

ቍጣዬንም እንዲፈጽሙ፣

ተዋጊዎቼን ጠርቻለሁ።

4በተራሮች ላይ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ

የሚሰማውን ጩኸት አድምጡ፤

በመንግሥታትም መካከል፣

እንደ ተጨናነቀ ሕዝብ ድምፅ የሆነውን ውካታ ስሙ!

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ሰራዊቱን ለጦርነት አሰልፏል።

5እግዚአብሔርና የቍጣው ጦር መሣሪያ፣

ምድሪቱን በሙሉ ለማጥፋት፣

ከሩቅ አገር፣

ከሰማያትም ዳርቻ መጥተዋል።

6የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና አልቅሱ፤

ሁሉን ቻይ13፥6 ዕብራይስጡ ሻዳይ ይላል። ከሆነ አምላክ ዘንድ ጥፋት ይመጣልና።

7ስለዚህ እጆች ሁሉ ሽባ ይሆናሉ፤

የሰውም ሁሉ ልብ ይቀልጣል።

8ሽብር ይይዛቸዋል፤

ሥቃይና ጭንቀት ይደርስባቸዋል፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት ያምጣሉ፤

እርስ በርሳቸው በድንጋጤ ይተያያሉ፤

ፊታቸውም በፍርሀት ቀይ ይሆናል።

9እነሆ፤ የእግዚአብሔር ቀን ጨካኝ ነው፤

ምድርን ባድማ ሊያደርጋት፣

በውስጧም ያሉትን ኀጢአተኞች ሊያጠፋ፣

ከመዓትና ከብርቱ ቍጣ ጋር ይመጣል።

10የሰማይ ከዋክብትና ሰራዊታቸው፣

ብርሃን አይሰጡም፤

ፀሓይ ገና ከመውጣቷ ትጨልማለች፤

ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም።

11ዓለምን ስለ ክፋቷ፣

ክፉዎችንም ስለ ኀጢአታቸው እቀጣለሁ፤

የትዕቢተኞችን እብሪት እሽራለሁ፤

የጨካኞችንም ጕራ አዋርዳለሁ።

12ሰውን ከነጠረ ወርቅ ይልቅ ውድ፣

ከኦፊርም ወርቅ ይበልጥ ብርቅ አደርጋለሁ።

13ስለዚህ በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር መዓት፣

ቍጣው በሚነድድበት ቀን፣

ሰማያትን እነቀንቃለሁ፤

ምድርንም ከስፍራዋ አናውጣለሁ።

14እንደሚታደን ሚዳቋ፣

እረኛም እንደሌለው የበግ መንጋ፣

እያንዳንዱ ወደ ወገኑ ይመለሳል፣

እያንዳንዱም ወደ አገሩ ይሸሻል።

15የተማረከ ሁሉ ይወጋል፤

የተያዘም ሁሉ በሰይፍ ይወድቃል።

16ዐይናቸው እያየ ሕፃናታቸው ይጨፈጨፋሉ፤

ቤታቸው ይዘረፋል፤ ሚስቶቻቸው ይደፈራሉ።

17እነሆ፤ ለብር ደንታ የሌላቸውን፣

በወርቅም ደስ የማይሰኙትን፣

ሜዶናውያንን አስነሣባቸዋለሁ።

18ቀስታቸው ጐበዞችን ይፈጃል፤

ሕፃናትን አይምሩም፤

ዐይናቸውም ለልጆች አይራራም።

19የመንግሥታት ዕንቍ፣

የከለዳውያን13፥19 ወይም፣ ባቢሎናውያን ማለት ነው። ትምክሕት

የሆነችውን ባቢሎንን፣

እግዚአብሔር እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ይገለብጣታል።

20በዘመናት ሁሉ የሚቀመጥባት አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም የለም፤

ዐረብ በዚያ ድንኳኑን አይተክልም፤

እረኛም መንጋውን በዚያ አያሳርፍም።

21ነገር ግን የምድረ በዳ አራዊት በዚያ ይተኛሉ፤

ቀበሮዎች ቤቶቿን ይሞላሉ፤

ጕጕቶች በዚያ ይኖራሉ፤

በበረሓ ፍየል የሚመሰሉ አጋንንትም ይዛለሉበታል።

22ጅቦች በምሽጎቿ፣

ቀበሮዎችም በተዋቡ ቤተ መንግሥቶቿ ይጮኻሉ፤

ጊዜዋ ቀርቧል፤

ቀኗም አይራዘምም።