弥迦书 7 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

弥迦书 7:1-20

以色列的败坏

1我真悲惨!

就像夏天的果子已被收尽,

葡萄已被摘净,

找不到一串可吃的,

寻不见我心中渴望的初熟无花果。

2虔敬人已从大地上灭绝,

世间再没有正直人。

人人伺机杀人流血,

用网罗猎取自己的弟兄。

3他们善于作恶。

领袖和审判官索要贿赂,

显贵袒露心中的恶欲,朋比为奸。

4他们当中最好的不过是蒺藜,

最正直的也不过是荆棘篱笆。

你们的守望者所说的日子,

就是你们受惩罚的日子已经来到。

你们必惊慌失措。

5不要相信邻居,

不要信赖朋友,

即使对你怀中的妻子也要守口如瓶。

6因为儿子藐视父亲,

女儿与母亲作对,

媳妇与婆婆作对;

家人之间反目成仇。

7至于我,

我要仰望耶和华,

等候拯救我的上帝;

我的上帝必垂听我的祈求。

8我的仇敌啊,

你们不要对我幸灾乐祸!

我虽跌倒,但必再爬起来;

我虽坐在黑暗里,

但耶和华必做我的光。

9我得罪了耶和华,

所以要忍受祂的惩罚,

直到祂为我辩护,替我申冤。

祂必领我进入光明,

我必亲睹祂的公义。

10从前嘲笑我说“你的上帝耶和华在哪里”的仇敌看见这事,

都必满面羞愧。

我必亲眼看见他们遭到报应,

他们要像街上的泥土一样被人践踏。

11以色列啊,

终有一日你会重建自己的城墙。

到那日,你必扩张自己的疆域。

12那日,从亚述埃及的各城,

埃及幼发拉底河,

从天涯到海角7:12 从天涯到海角”希伯来文是“从海到海,从山到山”。

人们都要到你这里来。

13然而,大地要因地上居民的罪恶而荒凉。

14耶和华啊,

求你用你的杖牧放属于你的羊群,

就是你的子民。

他们独自居住在丛林中,

住在肥沃的田园间。

愿他们像从前一样在巴珊基列吃草。

15耶和华说:

“我要向他们显出神迹奇事,

就像他们离开埃及时一样。”

16列国看见这一切,

都必因自己势力衰微而羞愧,

都必用手捂口,耳朵变聋。

17他们要像蛇一样舔土,

又如地上的爬虫,

战战兢兢地走出营寨;

他们必畏惧我们的上帝耶和华,

他们必对你充满恐惧。

18有何神明像你一样赦免罪恶,

饶恕你幸存子民的过犯?

你不会永远发怒,

因为你乐于施恩。

19你必再怜悯我们,

将我们的罪恶践踏在脚下,

把我们的一切过犯抛进深海。

20你必按古时给我们列祖的誓言,

以信实待雅各

以慈爱待亚伯拉罕

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 7:1-20

የእስራኤል መከራ

1ለእኔ ወዮልኝ!

የወይን ዕርሻ በሚቃረምበት ጊዜ፣

የበጋ ፍራፍሬ እንደሚለቅም ሰው ሆኛለሁ፤

የሚበላ የወይን ዘለላ የለም፤

የምንጓጓለት፣ ቶሎ የሚደርሰው በለስም አልተገኘም።

2ፈሪሀ እግዚአብሔር ያደረበት ሰው ከምድር ጠፍቷል፤

አንድም እንኳ ቅን ሰው የለም፤

ሰው ሁሉ ደም ለማፍሰስ ያደባል፤

እያንዳንዱም ወንድሙን በመረብ ያጠምዳል።

3እጆቹ ክፉ ለማድረግ ሠልጥነዋል፤

ገዥው እጅ መንሻ ይፈልጋል፤

ፈራጁ ጕቦ ይቀበላል፤

ኀይለኞች ያሻቸውን ያስፈጽማሉ፤

ሁሉም አንድ ላይ ያሤራሉ።

4ከእነርሱ ይሻላል የተባለው እንደ አሜከላ፣

እጅግ ቀና የተባለውም እንደ ኵርንችት ነው፤

የጠባቂዎቻችሁ ቀን ደርሷል፤

የእግዚአብሔር የፍርድ ቀን መጥቷል፤

የሚሸበሩበትም ጊዜ አሁን ደርሷል።

5ባልንጀራህን አትመን፤

በጓደኛህም አትታመን፤

በዕቅፍህ ለምትተኛዋ እንኳ፣

ስለምትነግራት ቃል ተጠንቀቅ።

6ወንድ ልጅ አባቱን ይንቃል፤

ሴት ልጅ በእናቷ ላይ፣

ምራት በዐማቷ ላይ ትነሣለች፤

የሰው ጠላቶች የገዛ ቤተ ሰዎቹ ናቸውና።

7እኔ ግን እግዚአብሔርን ተስፋ አደርጋለሁ፤

አዳኜ የሆነውን አምላክ እጠብቃለሁ፤

አምላኬ ይሰማኛል።

እስራኤል ትነሣለች

8ጠላቴ ሆይ፤ በእኔ ላይ በደረሰው ደስ አይበልሽ!

ብወድቅም እንኳ እነሣለሁ፤

በጨለማ ብቀመጥ እንኳ፣

እግዚአብሔር ብርሃኔ ይሆናል።

9እርሱን ስለ በደልሁ፣

እስኪቆምልኝ

እስኪፈርድልኝም ድረስ፣

የእግዚአብሔርን ቍጣ እቀበላለሁ፤

እርሱ ወደ ብርሃን ያወጣኛል፤

እኔም ጽድቁን አያለሁ።

10ጠላቴም ታያለች፤

ኀፍረትንም ትከናነባለች፤

“አምላክህ እግዚአብሔር የት አለ?”

ያለችኝን፣

ዐይኖቼ ውድቀቷን ያያሉ፤

አሁንም እንኳ፣

እንደ መንገድ ጭቃ ትረገጣለች።

11ቅጥሮቻችሁን የምትሠሩበት፣

ድንበራችሁንም የምታሰፉበት ቀን ይመጣል።

12በዚያ ቀን ሰዎች፣

ከአሦር እስከ ግብፅ ከተሞች፣

ከግብፅ እስከ ኤፍራጥስ፣

ከባሕር ወደ ባሕር፣

ከተራራ ወደ ተራራ ወደ እናንተ ይመጣሉ።

13ከሥራቸው የተነሣ፣

በነዋሪዎቿ ምክንያት ምድር ባድማ ትሆናለች።

ጸሎትና ውዳሴ

14ብቻቸውን በዱር ውስጥ፣

በለመለመ መስክ7፥14 ወይም በቀርሜሎስ መካከል የሚኖሩትን፣

የርስትህ መንጋ የሆኑትን፣

ሕዝብህን በበትርህ ጠብቅ፤

እንደ ቀድሞው ዘመን፣

በባሳንና በገለዓድ ይሰማሩ።

15“ከግብፅ እንደ ወጣህበት ዘመን ሁሉ፣

ታምራቴን አሳያቸዋለሁ።”

16አሕዛብ ያያሉ፣ ያፍራሉም፤

ኀይላቸውን ሁሉ ያጣሉ፤

አፋቸውን በእጃቸው ይይዛሉ፤

ጆሯቸውም ትደነቍራለች።

17በደረታቸው እንደሚሳቡ ፍጥረታት፣

እንደ እባብም ትቢያ ይልሳሉ፤

ከዋሻቸው እየተንቀጠቀጡ ይወጣሉ፤

በፍርሀትም ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለሳሉ፤

እናንተንም ይፈራሉ።

18የርስቱን ትሩፍ

ኀጢአት ይቅር የሚል፣ የሚምር

እንደ አንተ ያለ አምላክ ማነው?

ለዘላለም አትቈጣም፤

ነገር ግን ምሕረት በማድረግ ደስ ይልሃል።

19ተመልሰህ ትራራልናለህ፤

ኀጢአታችንን በእግርህ ትረግጣለህ፤

በደላችንንም ሁሉ ወደ ጥልቁ ባሕር ትጥላለህ።

20ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ

ለአባቶቻችን በመሐላ ቃል እንደ ገባህላቸው፣

ለያዕቆብ ታማኝነትን፣

ለአብርሃምም ምሕረትን ታደርጋለህ።