Забур 136 – CARS & NASV

Священное Писание

Забур 136:1-9

Песнь 136

1У рек Вавилона мы сидели и плакали,

когда вспоминали Сион.

2Там на вербах

мы повесили наши арфы.

3Там пленившие нас требовали от нас песен,

притеснители наши требовали от нас веселья,

говоря: «Спойте нам одну из песен Сиона».

4Как нам петь песнь Вечного

в чужой земле?

5Если я забуду тебя, Иерусалим,

то пусть отнимется моя правая рука.

6Пусть прилипнет язык мой к нёбу,

если не буду помнить тебя,

если не будет Иерусалим

моей самой большой радостью.

7Не забывай, Вечный, что делали эдомитяне

в день захвата вавилонянами Иерусалима,

как они говорили: «Разрушайте,

разрушайте его до основания!»

8Дочь Вавилона136:8 Дочь Вавилона – олицетворение Вавилона., обречённая на разорение!

Благословен тот, кто воздаст тебе

за то, что ты сделала с нами.

9Благословен тот, кто возьмёт и разобьёт

твоих младенцев о камень.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 136:1-26

መዝሙር 136

ምስጋና በቅብብሎሽ መዝሙር

1እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

2የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

3የጌቶችን ጌታ አመሰግኑ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

4እርሱ ብቻውን ታላላቅ ታምራትን የሚያደርግ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

5ሰማያትን በብልኀት የሠራ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

6ምድርን በውሃ ላይ የዘረጋ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

7ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

8ፀሓይ በቀን እንዲሠለጥን ያደረገ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

9ጨረቃና ከዋክብት በሌሊት እንዲሠለጥኑ ያደረገ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነው።

10የግብፅን በኵር የመታ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

11እስራኤልን ከመካከላቸው ያወጣ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

12በኀያል እጅና በተዘረጋች ክንድ ይህን ያደረገ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

13የኤርትራን ባሕር136፥13 ዕብራይስጡ ያመሱፍ የሚለው በ15 ከሚገኘው ጭምር የሸንበቆ ባሕር ይለዋል። ለሁለት የከፈለ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

14እስራኤልን በመካከሉ ያሳለፈ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

15ፈርዖንንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ያሰጠመ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

16ሕዝቡን በምድረ በዳ የመራ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

17ታላላቅ ነገሥታትን የመታ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

18ኀያላን ነገሥታትን የገደለ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

19የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን የገደለ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

20የባሳንን ንጉሥ ዐግን የገደለ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

21ምድራቸውን ርስት አድርጎ የሰጠ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

22ለባሪያው ለእስራኤል ርስት አድርጎ የሰጠ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

23በውርደታችን ጊዜ ያሰበን፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

24ከጠላቶቻችን እጅ ያዳነን፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

25ለፍጡር ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

26የሰማይን አምላክ አመስግኑ፤

ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።